con AA TEACHERS ASSOS1

con AA TEACHERS ASSOS1

Walia Tender ADMIN1 TAD

የጨረታ ማስታወቂያ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ልዩ ቦታው አቧሬ ወደ ቤልኤር ሆቴል በሚወስደው መንገድ ከጄነራል ሞተርስ አለፍ ብሎ ዋናው መንገድ ላይ 2B+G+6 ሆስፒታል እና 2B+G+9 ሁለገብ ሕንፃ ግንባታዎችን ለማሰራት የሥራ ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት አቅዷል፡፡

ስለሆነም በመጀመሪያው phase ለሚያሰራው 2B+G+9 ሁለገብ ሕንፃ ለማሰራት ስለሚፈልግ ተጫራቾች ለሥራው ሕጋዊ ፈቃድ ኖሯቸው የበጀት ዓመቱን ግብር የከፈሉ፣ የብቃት ማረጋገጫ የምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው፣ የተጨማሪ ዕሴት ታክስ ምስክር ወረቀት እንዲሁም በአቅራቢዎች ዝርዝር የተመዘገቡ BC-1andGC-1 የሆኑ የሥራተቋራጮች መሆን ይኖርባቸዋል፡፡

ተጫራቾች የጨረታሰነዱንቄራቡልጋሪያ መስቀለኛ መንገዱን ወረድ ብሎ በሚገኘው ኖክ (NOC) ማደያ ፊትለፊት ባለው ብርሃን መካከለኛ ክሊኒክ ግቢ ውስጥ በሚገኘው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ዋና ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እያሳወቅን ጨረታው በዚሁ ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 25 ተከታታይ ቀናት ድረስ የማይመለስ 500 ብር ( አምስት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ የሚችሉ መሆኑን እየገለፅን፤

ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በመሙላትና በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ (envelope) በማዘጋጀት የጨረታ መመሪያ በሚያዘው መሠረት ከላይ በተጠቀሰው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ዋና ጽ/ ቤት በተዘጋጀው የሰነድ ማስገቢያ ሳጥን ውስጥ ጨረታው በጋዜጣው ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስ ከ 26 ኛው ቀን ከ ረፋዱ 4፡30 ሰዓት ድረስ የጨረታ ሰነዱን (Technical & Financial Proposals) ለእያንዳንዱ አንድ ኦሪጂናልና ሁለት ኮፒ ማገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የቅድመ ብቃት ደረጃ ጨረታ ሰነድ (Original Technical & Financial Proposals) በዚሁ ዕለት ከረፋዱ 4 ፡30 ሰዓት ተዘግቶ ከ 15 ደቂቃ በኋላ ከረፋዱ 4 ፡45 ሰዓት ላይ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ቢሮ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት Original Technical & Financial Proposal ይከፈታል፡፡


ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መምህራን ማህበር ጽ/ ቤት



Posted:አዲስ ዘመን ግንቦት 25 ቀን 2012

Deadline: June 25, 2020


© walia tender

Report Page