Sale car ANRS PROC3
![](/file/f7c8077f1a42aa0a08e3c.jpg)
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡ አብክመ/ መግንማአ/ ብግጨ/ ዕግ/07/09/2012
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት ለተለያዩ ለክልል ሴክተር መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚውሉ
ሞተር ብስክሌቶች፣
የእሳት አደጋ መኪና፣
ትራክተር እና
ዳብል ጋቢና ተሽከርካሪ
በግልጽ ጨረታ አቅራቢዎችን በማሳተፍ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም አገልግሎቱ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቶችን ይጋብዛል፡-
በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ስራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
የግብር ከፋይነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
የግዥው መጠን ብር 200,000.00 (ሁለት መቶ ሺህ ብር) እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ከፋይነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
ተጫራቾች የማይመለ ስ ብር 200.00 / ሁለት መቶ ብር/ ብቻ ከግ ዥ፣ ፋይናንስና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 25 በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ከመንግስት ንብረት ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 6 መውሰድ ይችላሉ።
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ስለሚወዳደሩበት የተለያዩ ምድቦች (ሎቶች) ከዚህ በታች በተመለከተ ሰንጠረዥ መሠረት ተቀባይነት ባላቸው የአፈጻጸም ዋስትናዎች (Bid Bond) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያትዕዛዝ (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረት የባንክ ዋስትና (unconditional Bank Guarantee) ወይም በጥሬ ገንዘብ ANRS public procurement and property disposal service በሚል ስም ተዘጋጅቶ ማስያዝ አለባቸው::
![](/file/a52c6e49dd01159468ede.jpg)
ማንኛውም ተጫራች የቴክኒካልና ፋይናንሽያል የመጫረቻ ሰነዳቸውን በሁለት በተለያዩ ፖስታዎች ማለትም አንድ(1 ) ዋና (ኦርጅናል) እና አንድ (1) ቅጅ (ኮፒ) በማለት በጥንቃቄ በታሸጉ ፖስታዎች አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት በመንግስት ንብረት ግዥ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 6 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ከግንቦት 21 ቀን 2012 ዓ.ም እስከ ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
7. ጨረታው ሰኔ 22 ቀን 2012 ዓ. ም 4 ፡00 ሰዓት ታሽጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚህ ዕለት በ4 ፡30 ሰዓት በአብክመ የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት አዳራሽ ቁጥር 9 ይከፈታል፡፡
8. አገልግሎቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
9. በጨረታው ለመሳተፍ ለሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ቢሮ ቁጥር 6 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም
በፋክስ ቁጥር፡-0582262958 በመላክ ወይም
በስልክ ቁጥር፡- 058 220 1268/ 058 320 9841 /058 220 4509 በመደወል ማግኘት ይቻላል፡፡
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት የመንግስት ግዥና ንብረት ማስወገድ አገልግሎት
Posted: አዲስ ዘመን ግንቦት 21 ቀን 2012
Deadline: June 29, 2020
© walia tender