Pr st bu 2

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የግል ድርጅቶች ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና ኤጀንሲ ለ2012 በጀት ዓመት አገልግሎት የሚውሉ
የተለያዩ አላቂ የቢሮ ዕቃዎች/የጽህፈት መሳሪያዎች የፕሪንተር ቀለሞች፤ ፒቪሲ ካርዶች፤ የፕሪንተር ቀለም DTC 45000e/ሪባን/፤
የህትመት ውጤቶችን ብቻ ለአንድ ዓመት ውል በመያዝ፣ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ፡- የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንዲሳተፉ እንጋብዛለን፡፡
በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድና የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
የቫት ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
በመንግስት ግዥ ላይ ለመሳተፍ በግዥ ኤጀንሲ ድረ ገጽ ላይ የተመዘገበና ማስረጃ ማቅረብ የሚችል፣
ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ማስረጃ /ክሊራንስ/ ማቅረብ የሚችል፣
ማንኛውም ተጫራች ለእያንዳንዱ ሰነድ የ ማይመለስ ብር 100/ አንድ መቶ ብር/ በመክፈል ለዚሁ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው ለእያንዳንዱ ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ ቢድቦንድ በባንክ የተመሰከረ ቼክ /cpo/ ወይም የባንክ ዋስትና በኤጀንሲው ስም ማስያዝ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው አላቂ የቢሮ ዕቃዎች/የጽህፈት መሳሪያዎች የተለያዩ የፕሪንተር ቀለሞች፤ ፒቪሲ ካርዶች፣ የፕሪንተር ቀለም DTC 45000e/ሪባን፤ ሪባን/ ዕቃዎች ከመከፈቱ በፊት ሳምፕላቸውን/ናሙና/ ንብረት ክፍል ማቅረብ አለባቸው ::
ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው የህትመት ውጤቶች በኤጀንሲው ሳምፕል/ናሙና/ መሰረት የሚሰራ ስለሆነ ሰነድን በሚገዙበት ወቅት ሳምፕላቸውን/ናሙናውን/ ማየት አለባቸው፡፡
ተጫራቾች ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 የስራ ቀናት ጠዋት 2፡30-6፡30 ሰዓት ከሰዓት ከ7፡30-11፡30 ሰዓት ድረስ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የማወዳደሪያ ዋናውና ኮፒ ፖስታ በማለት ሰነዳቸውን ማስገባት ይችላሉ፡፡
ጨረታው የሚከፈትበ ት በ16 ኛው ቀን በ4 ፡00 ሰዓት ታሽጎ በተመሳሳይ ቀን በ4 ፡15 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም የእረፍት ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
በጨረታው አሸንፎ በወቅቱ ውል ለማያስሩ የጨረታ አሸናፊዎች ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ሲፒኦ አይመለስም፡፡
ኤጀንሲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
በጨረታ አሸናፊ ድርጅቶች የውል ማስከበሪያ ዋስትና 10% ሲፒኦ በማስያዝ ከመ/ቤቱ ጋር ውል የመፈራረም ግዴታ አለባቸው፡፡
አድራሻ አራት ኪሎ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት በስተጀርባ የቀድሞ ሲቪል ሰርቪስ ሚኒስቴር ህንጻ
ለበለጠ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር 011 1550366/011 157 0333 በፋክስ ቁጥር 011 155 0369

_______________________________
Category : Office Supplies and Stationery, Stationery Supplies, Printing and Publishing., Printing and Publishing Service, Purchase.
Posted Date : አዲስ ዘመን መጋቢት 29 ፥2012
Deadline :2020-04-22