Furn sale AAUCU1

Furn sale AAUCU1


የጨረታ ማስታወቂያ

ጨረታ ቁጥር አ / አ / ከ / ኤ // ግ / ጨ /011/2012

የአዲስ አበባ ከተማ ኤሌክትሪክ እገልግሎት የተለያዩ ዓይነት የፅህፈት መሳሪያዎች እና የስብሰባ ጠረጴዛ ከ30 (ሰላሳ) ወንበሮች ጋር (Conference Table With 30 seats) በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡

ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ፣ የተጨ.እታ ፣ የግብር ከፋይ መቁጥር እና ከገቢዎች ባለስልጣን ጽ/ቤት ጨረታ ላይ እንዲሳተፉ የሚል ማስረጃ ያለው በጨረታው መሳተፍ ይችላል፡፡

ተጫራቾች የመንግስት ድርጅቶች በሚያወጡት ጨረታ ላይ ለመሳተፍ እንዲችሉ በግዥ ኤጀንሲ ድረ-ገፅ ላይ የተመዘገቡ መሆኑን ማረጋገጫ ማቅረብ አለባቸው::
በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ ከላይ የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች በማያያዝ መወዳደር የሚችሉ ሲሆን ዝርዝር ሁኔታው በጨረታ ሰነዱ ውስጥ ይገኛል፡፡

ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ለሎት-1 እና ሎት-2 ለእያንዳንዳቸው ብር 200.00 ( ሁለት መቶ) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡

አድራሻ፡-ሃያ ሁለት ድንበሯ ሆስፒታል ፊት ለፊት በሚገኘው በአዲስ አበባ ከተማ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ግዥ ፣ ሎጀስቲክስ፣ ዌርሀውሲንግ እና ፋሲሊቲ ቢሮ፣
ተጫራቾች ለጨረታ ዋስትና ማስከበሪያ የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን ከላይ በሠንጠረዡ ውስጥ በተገለፀው መሠረት ሆኖ በባንክ በተረጋገጠ ቼከ/CPO/ ወይም በቅድመ ሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ለስድስት ወራት የሚያገለግል የባንክ ዋስትና (Bid Bond) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡

ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ ቴክኒካል «ኦሪጅናል እና ኮፒ ፋይናንሻል ኦሪጅናል እና ኮፒ በማለት በተለያየ ፖስታ በማሸግ እና ሁለቱን በአንድ ትልቅ ፖስታ በማድረግ ጨረታ ቁጥር አ/አ/ከ/ኤ/አ/ግ/ጨ/005/2012 ሎት-1 እና ሎት-2 የሚል ምልክት በማድረግ እስከ ሰኔ 09 ቀን 2002 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፣
ጨረታው ከላይ በተገለፀው መሠረት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል ፣

ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0116-36-60-52/0116-366003 መደወል ይችላሉ፡፡

ድርጅቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

የአዲስ አበባ ከተማ ኤሌክትሪክ አገልግሎት



Posted:አዲስ ዘመን ግንቦት 23 ቀን 2012
Deadline: June 16, 2020


© walia tender

Report Page