DCCH
DOCH HDየዳውሮ የባህል፣የቋንቋና ታሪክ ምርምር ማዕከል አካል የሆነው የባህል አዳራሽ ግንባታ ሥራ ዳግም ለማስጀመር የሚያስችል ስምምነት ላይ መደረሱን የዳዉሮ ዞን ዋና አስተዳደር አስታውቋል።
የግንባታው ሂደት ለአጭር ጊዜ ተቋርጦ መየቆቱ በህብረተሰቡ ዘንድ ቅሬታን ሲፈጥር መቆየቱም ተጠቁሟል።
የአዳራሽ የግንባታው ሂደት ከተቋረጠ ሰባት ወራትን ያስቆጠረ ሲሆን ግንባታው በህብረተሰቡ የነቃ ተሳትፎ የሚገነባ እንደመሆኑ በመቋረጡ ምክንያት በኅብረተሰቡ ዘንድ ቅሬታን ሲፈጥር ነበር።
የፕሮጀክቱ ግንባታ በታዎር ኮንስትራክሽን የሕንጻ ስራ ተቋራጭ ሲካሄድ እንደነበረ የሚታወስ ሲሆን ይህ የሥራ ተቋራጭ የግንባታ ሂደት በማዘግየት፣ የግንባታውን ሕግ እና ሥርዓት ያልተከተለ የዋጋ ጭማሪ በመጠየቅ እና ውሉን በገዛ ፍቃዱ በማቋረጡ ምክኒያት ግንባታው እንድዘገይ ተደርጓል።
በተፈጠረው አለመግባባት የክስ ሂደት ውስጥ በመገባቱና የንብረት ቆጠራ ጊዜ የወሰደ ቢሆንም ግንባታው ተጠናቅቆ ለአገልግሎት እንዲበቃ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመተባበር አሁን ላይ ማስቀጠል የሚያስችሉ ተግባራትን ማከናወን ተችሏል።
የዳውሮ ባህል ማዕከል አዳራሽ ግንባታ በአጭር ጊዜ እንዲጠናቀቅ የመንግሥት ልማት ድርጅት ከሆነው ከኦሮሚያ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ጋር አሰራሩን ጠብቆ ቀሪ ሥራ እንደሚጠናቀቅም ተገልጿል።
ግንባታው አሁን ያለበት ደረጃ 22.9% ላይ ብቻ በመሆኑ የግንባታው ቀሪ ስራዎች የምህንድስና ግምት ዋጋ 3 መቶ 85 ሚሊዮን 5 መቶ 09 ሺህ 26 ብር ሲሆን፣ በምህንድስና ግምቱ ዋጋ በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ግንባታውን እንዲያጠናቅቅ የሚያስችል የውል ስምምነት ተደርሷ።
የዳውሮ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳዊት ገበየሁ እንደገለጹት የዳውሮ ዞን የባህል ማዕከል አዳራሽ ግንባታ የዳውሮ ልማት ወዳድ ማኅበረሰብ እና አጋሮቹ በልዩ ትኩረት የበኩላቸውን ድርሻ እያበረከቱ መቆየታቸውን ገልፀዋል ።
ይህ የተቋረጠው ግንባታ እንደገና እንዲጀመር የዳውሮ ልማት ማህበር የበላይ ጠባቂ ፣ የቦርዱ አባላትና በየደረጃው የሚገኙ አመራር አካላት ላቅ ያለ አስተዋጽኦ ማበርከታቸውንም ገልጸዋል።
የዳውሮ ልማት ማህበር ቦርድ በበኩሉም ከፍርድ ቤት ለቀረበልን ክስ አማካሪያችንና የህግ ባለሙያዎችን በማማከር ምላሽ በመስጠት እና በግንባታ ዙሪያ የሚፈጠሩ አለመግባባቶች እንዲፈቱ ከፌደራል ኮንስትራክሽን ባለሥልጣን በድርድር አማራጭ ጉዳዩ እንዲያልቅ ሀሳብ መሰጠቱን ዋና አስተዳዳሪው አክለዋል ።
ባለስልጣን መስሪያ ቤቱ ሂደቱን እንድመራና ኮንትራክተሩ፣ አማካሪው፣ የክልልና የዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን መሃንዲሶች፣ የፀጥታ ፣ ፍትህ አካላትና ሌሎች ባለድርሻ አካላት በተገኙበት የሳይት ቆጠራ መደረጉንም ጠቁመዋል።
አዲስ ሳይቱን የተረከበው ድርጅት የመንግስት የልማት ድርጅት መሆኑ ለቀጣይ የህዝብ ለህዝብ ትስስር ከፍተኛ ሚና የሚኖረው እንድሁም ካለው ልምድና አቅም አንፃር ግንባታውን በተሻለ ጥራትና ውል ከገባው ጊዜ አስቀድሞ በማጠናቀቅ የዘወትር አጋርነቱን በተግባር እንደሚያሳይ እምነታችን የፀና ነው ብለዋል።
የግንባታው ሂደቱ በተጓተተበት ወቅትም ቢሆን በትዕግስት የጠበቁ የብሔሩ ተወላጆችንና የልማቱ አጋሮችን እንዲሁም የግንባታው ሂደት ዳግም እንዲጀመር የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ላበረኩቱት በሙሉ የዞኑ አስተዳደር በዳውሮ ሕዝብ ስም ከፍ ያለ ምስጋና አቅርበዋል።