Con machinery 5

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ክልል በደቡብ ወሎ ዞን ከላላ ወረዳ ልጓማ ከተማ መሪ ማዘጋጃ ቤት በ2012 በጀት ዓመት የውስጥ ለውስጥ መንገድ ለማሰራት የማሽን ኪራይ ይፈልጋሉ፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩት ማሸኖች እስከ ዝርዝር መገለጫቸው ያሟሉና የተገለፀ ዝርዝር መስፈርቶችን የምታሟሉ ተጫራቾች በጨረታ መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የማሽኖቹ አይነት
1ኛ ኤክስካቫተር Cat 325 ፣
2ኛ ቡል ዶዘር D8R እና ከዚያ በላይ
3ኛ ሞተር ግሬደር/40 h cat
4ኛ ቫይብራቶሪ ሮለር 14 ቶን እና ከዚያ በላይ
5ኛ ውተር በውሰር (ሻወር ትራክ)
6ኛ ዳምፕ ትራክ (SINO TRUCK) 14 ሜ3 እና ከዚያ በላይ የሚይዝ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ማሽኖች ከ2008 እኤእ ወዲህ የተመረቱ ምርት ማቅረብ የሚችል ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟላ ተጫራቾች መወዳደር ይችላሉ፡፡
ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑ ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ቲን ነምበር ማቅረብ የሚችል፡፡
የግዥ መጠን ብር 100,000 / አንድ መቶ ሺህ ብር / በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ፣ የካት ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፡፡
እያንዳንዱ ዋጋ የሚሞላው በነፃ ገበያ ላይ ተመስርቶ መሆን አለበት፡፡
ተጫራቾች የማሽን የቴክኒክ ብልሽት፣ የስፔር ፓርት ለውጥ እንዲሁም ዘይት ነክ ነገሮች እና የነዳጅ ወጭ ተጫራቹ የሚችል፡፡
የማሽን ኪራይ ሰዓት የሚይዘው ለሰራው ስራ ሰዓት ብቻ ነው (የተፈጥሮ ኤደጋዎች ዝናብ እና ተያያዥ ችግሮች ከተከሰቱ፡ የሚባከነው ሰዓት አይያዝም፡፡
የማሽን መጓጓዣ እና መጫን ማውረጃ እንዲሁም ከሚሰራበት ቦታ (ሳይት) ወደ ሌላ ሳይት መጓጓዣ መጫን ማውረጃ ተጫራቹ የሚችል ይሆናል፡፡
ተጫራቾች የሹፌር እና የኦፕሬተር እንዲሁም የረዳት እስል እና ሌሎች ወጭዎች ተጫራቹ የሚሸፍን፡፡
ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-7 የተጠቀሱትን ለሚመለከታቸው ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከጨረታ ሰነዱ ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
የዕቃው ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ ወይም እስፔስፍኬሽን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 ( ሁለት መቶ ብር) በመክ ፈል በመ/ቤታችን ቢሮ ቁጥር 1(አንድ) ሰነዱን መግዛት ይቻላል፡፡
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ወይም የጨረታ ማስከበሪያ ለሚወዳደሩበት ብር ወይም የዕቃውን ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋ ገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ») ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ በመ/ቤቱ ደረሰኝ በመሂ 1 ማስያዝ ያለባቸውና የአሸናፊነት ደብዳቤ ከተፃፈለት ቀን ጀምሮ በ5 የስራ ቀናት ውል መግባት ያለበት ሲሆን የወል ማስከበሪያ 10 በመቶ ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት፡፡
ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም ኣንድ ወጥ በሆነ እርጅናል ፖስታ በጥንቃቄ በማሸግ በከላላ ወረዳ ልጓማ መሪ ማዘጋጃ ቤት በግ/ፋ/ን/አስ/ደ/ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 ኣንድ በተዘጋጀ የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እንዲሁም ቅዳሜና እሁድ ጭምር ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
ጨረታው በጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታያ ቀናት በአየር ላይ ቆይ ቶ በ16 ኛው ቀን በ3 ፡30 ሰዓት ይዘጋል፡፡ በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገ ኘበት በ4 ፡30 ሰዓት ይከፈታል ነገር ግን በበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው በስራ ቀን ይከፈታል፡፡
መ/ቤቱ በጨረታው የሚሰሩ ስራዎች ላይ ብዛት የመጨመር ሆነ የመቀነስ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማንኛውም ተጫራቶች በሌላ ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፡፡
ማንኛውም ተጫራቾች ግዥው በጥቅል /በሎት/ የሚፈፀም መሆንን አውቆ ለእያንዳንዱ ዝርዝር እቃዎች ዋጋ መሙላት ይኖርበታል የተዘረዘሩት ዕቃዎች በሙሉ ጠቅላላ ለእያንዳንዳቸው ዋጋ ያለመሙላት ከጨረታው ውድቅ ያደርጋል፡፡ ሆኖም ግን ግዥው በጥቅል ወይም በሎት ቢሆንም መ/ቤቱ የተጋነነ ዋጋ የተሞላባቸው ስራዎች ከሎት ውስጥ ነጥሎ በማውጣት ዝቅተኛ ዋጋ ካቀረቡበት አቅራቢዎች በለቀማ ማሰራት እንደሚቻል መታወቅ አለበት፡፡ እንዲሁም አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሽነፉባቸውን ስራዎች ሙሉ በሙሉ ሰርቶ ካላስረከበ ክፍያ የማይፈፀም መሆኑን
መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 033-4550029 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
ማሳሰቢያ፦
ወደ ስራ ከገቡ በኋላ ናፍጣ የሚሞላው በተቋራጩ ይሆናል
ከመንገዱ እስከ ኳሪ ሳይት ያለው ርቀት ከ 0 እስከ 5 ኪሜ የሆነ
በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት
በደቡብ ወሎ መስተዳደር ዞን ከላላ
ወረዳ ልጓማ ከተማ መሪ ማዘጋጃ
Posted: አዲስ ዘመን ግንቦት 05 ቀን 2012
Deadline: May 28, 2020
© walia tender