Con 50

የጨረታ ማስታወቂያ
የደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት የግዥና ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን
ሎት 1 ቀበሌ 01 ሊዝ ሰፈር ካልቨርት እና ቀበሌ 02 ከብሩህ ተስፋ ት/ቤት እስከ ወጣት ማዕከል ስላቭ ስራ በፓኬጅ ቁጥር D/CW-07/2019/2020 በUIIDP በጀት ደረጃ 8 እና በላይ የሆነ በጠቅላላ ስራ ተቋራጭ/GC/ ወይም በመንገድ ለራ ተቋራጭ RC የሆኑ ስራ ተቋራጮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
ስለዚህ በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው እና በ2012 የታደለ የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች በጡረታ መሳተፍ ይችላሉ፡፡
በ2012 በጀት ዓመት የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው ወይም የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ
የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር Tin Number/ ያላቸው
የግዥ መጠኑ ከብር 50000 /ሀምሣ ሺህ ብር/ እና በላይ ከሆኑ የተጨማሪ እሴት ታክስ ቫት/ ከፋይነት የተመዘገቡ ማሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል፣
ተጫራቾች ከአማራ ክልል ውጭ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ከሆነ በ2012 በጀት ዓመት የታደሰ የፌዴራል የብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ከዋናው ጋር የተገናዘበ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻው ሰነዶች ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡ ተጫራቾች የመጫረቻ ዋጋቸውን መ/ቤቱ ባዘጋጀው የጨረታ ዋጋ ማቅረቢያ ቅፅ ሞልተው ማቅረብ አለባቸው፡፡
የግንባታዎቹን የስራ ዝርዝር መግለጫ /Specification/እና መወዳደሪያ መስፈርቶቹን ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ።
በጨረታው ሰነድ ላይ ስርዝ ድልዝ ወይንም ለመለየት አሻሚ የሆነ ጽሁፍ መኖር የለበትም
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ደጋፊ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 ድረስ በመምጣት ለእያንዳንዱ ጨረታ የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን ገዝተው መጫረት ይችላሉ፡፡
ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ብር 20,720/ሀያ ሺህ ሰባት መቶ ሃያ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና /ጋራንት በስማቸው ለደብረ ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት በሚል አድራሻ ከኦርጅናል ሰነዱ ጋር አብሮ በአለባቸው። የጨረታ ማስከበሪያ ፀንቶ የሚቆይበት ጊዜ ጨረው ከተከፈተበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 30 ቀናት ይሆናል።
ማንኛውም ተጫራች ለሚወዳደሩበት የግንባታ ጨረታ ህጋዊ ማስረጃዎቹን እና የጨረታ ሰነዱን በአንድ ላይ በማድረግ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶችና ኮንስትራክሽን አገልግሎት ጽ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 29 ተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስታወቂያው በጋዜጣ በግልፅ ጨረታ ከወጣበት እለት ጀምሮ በ30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
ጨረታው በጋዜጣ ግልፅ ጨረታ ከወጣበት ቀን በ31ኛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደ/ብ/ከ/አስ/ከ/ል/ቤ/ኮ/አገ/ጽ/ቤት ግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 29 በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል ። ዕለቱ ቅዳሜ እሁድ ወይም የህዝብ በዓላት ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት 4፡30 ይከፈታል፡፡ ሆኖም ተጫራቾች በራሳቸው ምክንያት ባይገኙ የጨረታው ፖስታ ተሟልቶ ከተገኘ እንዲከፈት በማድረግ ውድድሩ ይካሄል ።
አሸናፊው ተጫራች ውጤት ከተለፀበት ቀን ጀምሮ ከ5 የስራ ቀን በኃላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀን ውስጥ የሚፈለጉበትን ማስረጃዎች በማቅረብ ውለታ መፈፀም ይኖርበታል
በጨረታው አሸናፊ የሆነ የውል ማስከበሪያ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ/10%/ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.ኦ/CPO/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትናሕይኖራል፡፡
መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ወይም ኦማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብት አለው
በማስታወቂያው ያልተገለፁ ነገሮች ቢኖሩም በገዥ መመሪያው መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
ተጫራቾች ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት በስልክ ቁጥር፡- 011 681 2717/28 57 ላይ በመደወል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የደ/ብርሃን ከተማ አስተዳደር ከተማ አስተዳደር ከተማ ልማት ቤቶች ኮንስትራክሽንና አገልግሎት ጽ/ቤት የግ/ፋ/ን/አስ/ቡድን
posted date:አዲስ ዘመን መጋቢት 18፥2012
dead line:April 27,2020 (ሚያዝያ 19 በ4:00 ሰአት)