Car haraj birhan42
የሐራጅ ማስታወቂያ
ብርሃን ባንክ አማ ከባለእዳዎቹ ላይ ለሚፈልገው ገንዘብ በዋስትና የያዛቸውን እና ከዚህ በታች የተመለከቱትን ንብረትቶች በአዋጅ ቁጥር 97/1990 እና በተሻሻለው 216/92 ለባንኮች በተሰጠው ስልጣን መሠረት ባሉበት ሁኔታ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል :: ተጫራቾች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች በመገንዘብ ማክበር ይኖርባቸዋል::
ተጫራቾች የጨረታ መነሻ ዋጋውን የ1/4 ( አንድ አራተኛ) በ ባንክ በተረጋገጠ ቼክ(ሲፒኦ) በብርሃን ባንክ አማ ስም ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ::
የጨረታው አሸናፊ ጨረታውን እንዳሸነፈ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ያሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ በ15 (አስራ አምስት) ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ከፍሎ ንብረቱን መረከብ አለበት:: በእነዚህ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካልከፈለ ጨረታው ተሰርዞ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ይሆናል:: በጨረታው ለተሸነፉት ተጫራቾች ያስያዙት ሲፒኦ ይመለስላቸዋል::
የመኖሪያ ቤቶቹ ጨረታ ንብረቱ በሚገኝበት ቦታ ይከናወናል የተሽከርካሪው ጨረታ የሚከናወነው በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 03 በሚገኘው ወመሳኮ ሕንፃ 5ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 509 ይሆናል:: የጨረታ አሸናፊው በሚገዛው ንብረት ላይ ለመንግስት የስም ማዛወሪያ ክፍያዎች ፣ የሊዝ ፤ የግብር እና ሌሎች ክፍያዎች ይመለከተዋል::
መያዣ ሰጪዎች ሐራጁ በሚከናወንበት ቦታ ቀንና ሰዓት መገኘት ይችላሉ:: ባይገኙ ግን ሐራጁ በሌሉበት ይካሄዳል::
ለጨረታ የቀረቡትን ንብረቶች በስራ ሰዓት ኘሮግራም አስይዞ ለመጐብኘት ይቻላል::
ባንኩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው::
ብርሃን ባንክ አ.ማ
Posted: ሪፖርተር ግንቦት 17 ቀን 2012
Deadline: June 28, 2020
© walia tender