Bui 33 ecwc33
![](/file/50c18b8c5e1693fe8a617.jpg)
የጨረታ ማስታወቂያ
ጨ/ ቁጥር ኢኮስኮቲ-58/2012
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ባለ 12.00*24 መግዛት ስለሚፈልግ በአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ብቁ ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
በጨረታው ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው ነገር ግን በአቅራቢዎች ዝርዝር ያልተመዘገቡ ተጫራቾች ለሚመለከተው የመንግስት መ/ቤት በማመልከት የምዝገባ ሰርተፍኬት ማግኘት ይችላሉ፡፡
የመጫረቻ ሰነዱ የሚዘጋጀው በእንግሊዘኛ ቋንቋ ነው፡፡
የጨረታው አሸናፊ የሚሆነው በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተመለከቱት መስፈርቶች መሠረት ሲሆን ጨረታው ዜግነትን ሳይመለከት ለማንኛውም አቅራቢ ክፍት ነው፡፡ የጨረታው ሰነድ የተዘጋጀው በእንግሊዘኛ ቋንቋ ነው ፡፡
ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ጨረታ ከጠቅላላ የመጫረቻ ዋጋ ከ1% ያላነሰ ወይም ከብር 500,000.00 ያልበለጠ የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይንም በባንክ ዋስትና ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ወጪ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልክ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም፡፡
ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ለዚህ ተግባር በተዘጋጀው ሳጥን የሀገር ውስጥ ጥቅል ግዥ ቡድን ገቢ የሚያደርጉበት የመጨረሻ ቀን ግንቦት 25 ቀን 2012 ዓ. ም እስከ ጠዋቱ 4 ፡00 ሰዓት ድረስ ብቻ ነው::
ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻው በተገኙበት ግንቦት 25 ቀን 2012 ዓ. ም ከጠዋቱ 4 ፡30 ሰዓት ላይ የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ቅጥር ግቢ በሚገኘው የሀገር ውስጥ ጥቅል ግዥ ቡድን የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ለበለጠ መረጃ ተጫራቾች የሚከተለውን አድራሻ መጠቀም ይችላሉ፡፡
ጥቅል ግዥ ቡድን
ፓስታ ሳጥን ቁጥር 21952/1000
የስልክ ቁጥር 0118962991/0118723086
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
የኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን
Posted:አዲስ ዘመን ግንቦት 11 ቀን 2012
Deadline: June 2, 2020
© walia tender