Agri 5

Sugar Corporation
የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር MSF/LP/03/2020
በስኳር ኮርፖሬሽን የመተሐራ ስኳር ፋብሪካ ከዚህ በታች የተገለፀውን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ጥቅል አንድ፡- የውሃ ማጣሪያ ፕላንት (Water Treatment Plant)
ጥቅል ሁለት፡- የስኳር ማሸጊያ ከረጢት (Sugar bags of 100 kg for commercial sugar Bagging)
በመሆኑም ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
ሕጋዊ የንግድ ሥራ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን የሀገር ውስጥ ገቢ ግብር አጠናቀው የከፈሉና ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው ድርጅቶች የማይመለስ ብር ለጥቅል አንድ 200 ( ሁለት መቶ ብር) ለጥቅል ሁለት 100 ( አንድ መቶ ብር) በመክፈል ዘወትር በሥራ ሰዓት ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ህንፃ ግዥ ቡድን 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 220 የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ገዝተው በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡
ተጫራቶች ከሚያቀርቡት ሠነድ ጋር የታደሰ የንግድ ፈቃድ የአቅራቢዎች የምዝገባ ሠርተፊኬት እና ለጨረታ ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ቢያንስ 2% በሲፒኦ ማቅረብ አለባቸው፡፡
ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ በራሳቸው የዋጋ ማቅረቢያ (Performa invoice) ላይ በማዘጋጀት በሰም በታሸገ ፖስታ በማድረግ እ.ኢት.ኢ ሚያዝያ 15 ቀን 2012 ዓ. ም እስከ ጠዋቱ 4 ፡00 ሰዓት ድረስ ሜክሲኮ ፊሊፕስ ሕንፃ ቢሮ ቁጥር 119 ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ጨረታው በዕለቱ ሚያዝያ 15 ቀን 2012 ዓ. ም ከጠዋቱ 4 ፡30 ሰዓት ላይ ከላይ በተጠቀሰው አድራሻ ቢሮ ቁጥር 119 ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
ፋብሪካው ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ስልክ ቁጥር 011550 56 07/ 0115-50 5821
ሜክሲኮ አደባባይ ፊሊፕስ ሕንፃ
አዲስ አበባ
በስኳር ኮርፖሬሽን የመተሐራ
ስኳር ፋብሪካ
_______________________________
Category : Agriculture, Agricultural Raw Material and Supplies, Laboratory and Chemicals, Chemicals and Reagents, Plastic/ Pipes and Fittings, Purchase.
Posted Date : አዲስ ዘመን መጋቢት 10 ቀን 2012
Deadline :2020-04-23