*/

*/

Source

ፈረንሳይ ኢትዮጵያ ሰላምና ፀጥታን ለማስከበር የምታከናውነውን ስራ እንደትምደግፍ አስታወቀች *************

(ኢ.ፕ.ድ)

ፈረንሳይ ኢትዮጵያ ሰላምና ፀጥታን ለማስከበር የምታከናውነውን ስራ እንደትምደግፍ አስታወቀች።

በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የውጭ ግንኙነትና የሰላም ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ በኢትዮጵያ የፈረንሳይ አምባሳደር ሬሚ ማሬሾን የተመራ ልዑካን ቡድን በጽህፈት ቤታቸው ተቀብለው አነጋግረዋል።

ዶክተር ነገሪ ሌንጮ በዚሁ ወቅት፥ ፈረንሳይ ለኢትዮጵያ ለምታደርገው ሁለንተናዊ ትብብር አመስግነው፣ የቀጠናውን ሰላምና ጸጥታ ለማስፈንና ከመቸውም ጊዜ በበለጠ አስተማማኝ ለማድረግ ኢትዮጵያ ከፈረንሳይ ጋር እንደምትሰራ አብራርተዋል።

ሰብሰቢው አክለውም በኢትዮጵያ የተከናወነውን የሕግ ማስከበር ዘመቻ አስመልክተው ለአምባሳደር ሬሚ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

በማብራሪያቸውም በዴሞክራሲ ስም ለ27 አመታት የኢትዮጵያን ሕዝብ ሲያሰቃይ የነበረው አምባገነኑ ህወሓት ላይ የተወሰደው ሕግን የማስከበር ዘመቻ ከሁለት ቀናት በፊት መጠናቀቁን ገልጸዋል።

በህግ ማስከበር ዘመቻው ከቀያቸው ተፈናቅለው በሱዳን የሚገኙ የሕብረሰብ ክፍሎችን መልሶ ለመቋቋም መንግስት በትኩረት እየሰራ መሆኑንም አብራርተዋል።

የፈረንሳይ አምባሳደር ሬሚ ማሬሾን በበኩላቸው፥ ፈረንሳይ ሰላምና ጸጥታን ለማስከበር ከኢትዮጵያ ጋር በትብብር እንደምትሰራ አረጋግጠዋል።

በቀጠናው ሰላምና ጸጥታን ለማስፈን ኢትዮጵያ ሽብርተኝነትን በመዋጋት ረገድ የምታደርገውን ጥረት አምባሳደሩ አድንቀው፤ ፈረንሳይ በወታደራዊ ትብብር ጭምር ከኢትዮጵያ ጎን በመሆን እንደምትሰራ መግለፃቸውንም ከምክር ቤቱ ጽህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

Report Page