እንደሰው አይደለም - ኢየሩሳሌም ነጊያ

እንደሰው አይደለም - ኢየሩሳሌም ነጊያ


Eyerusalem Negiya‎ | Qen Sale

እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ ቢሆን ፡ ኖሮ

እንደ ፡ ሰው ፡ ቢያስብ ፡ ኖሮ

ኃጢአቴን ፡ ልናዘዝ ፡ ህሊናዬ ፡ ሲወቅሰኝ

ምህረትም ፡ ልማጠነው ፡ ደጅ፡ ባስጠናኝ

ውድቀቴ ፡ ሳይገደው ፡ ባላገጠ ፡ ፊቱ ፡ በጠቆረ

ፍቅሩ ፡ ቀዝቅዞብኝ ፡ ድምጹ ፡ በሻከረ


እንኳንስ ፡ ልጁ ፡ ሊያረገኝ

ሥሙን ፡ ለመጥራት ፡ ባስከፈለኝ (፪x)

እንኳንስ ፡ ቤቱ ፡ ለመኖር

ከደጁ ፡ መጣል ፡ በተሳነኝ

ከደጁ ፡ መጣል ፡ በናፈቀኝ


አዝ፦ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም

ከቶ ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም

ምህረት ፡ ቸርነቱ ፡ ወሰን ፡ ቁጥር ፡ የለው

ከወዳጅም ፡ ወዳጅ ፡ ፍቅሩ ፡ ብዙ ፡ ነው

እግዚአብሔር ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ እንደ ፡ ሥጋ ፡ ለባሽ

የወደቀን ፡ አይቶ ፡ እንዳላየ ፡ አይሸሽ


እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም (፬x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም


እግዚአብሔር ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ ቢያይ ፡ ኖሮ

እንደ ፡ ሰው ፡ ቢያስብ ፡ ኖሮ

ያለኝን ፡ ሁሉ ፡ ሳጣ ፡ ሲጐድል ፡ ሙሉ ፡ ቤቴ

ከንፈር ፡ ቢመጥልኝ ፡ ርቆ ፡ ከአጠገቤ

ባሕሪው ፡ ተለውጦ ፡ ቀስ ፡ እአለ ፡ በሽሽ ፡ በራቀ

ወዳጅነት ፡ ቀርቶ ፡ አዛኝ ፡ በመሰለ


ነፍሴን ፡ ሲከፋት ፡ ዝም ፡ ስል

ሃዘኔ ፡ ንቀት ፡ ቢመስል (፪x)

ውስጤ ፡ ማቅ ፡ ለብሶ ፡ ከሰው ፡ ቢያርቅ

እንደኮራሁ ፡ ቢያስበኝ ፡ እንደተኩራራሁ ፡ ቢያስበኝ


አዝ፦ ግን ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም

ከቶ ፡ እግዚአብሔር ፡ እንደሰው ፡ አይደለም

ምህረት ፡ ቸርነቱ ፡ ወሰን ፡ ቁጥር ፡ የለው

ከወዳጅም ፡ ወዳጅ ፡ ፍቅሩ ፡ ብዙ ፡ ነው

እግዚአብሔር ፡ እንደ ፡ ሰው ፡ እንደ ፡ ሥጋ ፡ ለባሽ

የወደቀን ፡ አይቶ ፡ እንዳላየ ፡ አይሸሽ


እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም (፬x)

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ ፍቅሩ ፡ አያረጅም

እንደ ፡ ሰው ፡ አይደለም ፡ አይለዋወጥም



Report Page