ስለምሕረትህ
Muluken Meleseስለምሕረትህ ስለጥበቃህ ስለውለታህ ጌታ ሆይ ምንስ ልክፈልህ
ከበርት ወይፈኑን ከአዝርትም ምርጡን
ከሐብት ከበረክት ከአስራት ምጽዋቱን
ነፍሰእንም ጨምረእ ሚዛን ላይ ብሰፍረው
ጌታ ለውለታህ እጅግ ያነሰ ነው
በተለምዶ ቃላት ተመስገን ልበልህ
ሌላማ ምን አለኝ ላንተ የምሰጥህ
አምላክ ሆይ ውለታህ እጅግ የበዛ ነው
ቤት አልሰራልህም ዙፋንህ ሰማይ ነው
ብር ወርቁ ያንተ ነው ምን እሰጥሃለሁ
ብቻ በአንደበቴ ተመስገን እላለሁ
እንደዳዊት ልዝለል ልዘምር ልጨፍር
አዳኝነትህን ገድልህን ልናገር
ጌታ ለውለታህ የለም የምከፍልህ
የኔ ታሪክ ድርሻ አንተን ማሞገስ ነው
ሐጥያት መስራት ትቼ ወዳንተ ብመለስ
በአለም ዙሪያ ሮጬ ወንጌልን ባዳርስ
ሰማይና ምድርን እንደ ንስር ባስስ
ጌታ ውለታህን አልችልም ልመልስ