ስለምሕረትህ

ስለምሕረትህ

Muluken Melese

ስለምሕረትህ ስለጥበቃህ ስለውለታህ ጌታ ሆይ ምንስ ልክፈልህ


ከበርት ወይፈኑን ከአዝርትም ምርጡን

ከሐብት ከበረክት ከአስራት ምጽዋቱን

ነፍሰእንም ጨምረእ ሚዛን ላይ ብሰፍረው

ጌታ ለውለታህ እጅግ ያነሰ ነው

በተለምዶ ቃላት ተመስገን ልበልህ

ሌላማ ምን አለኝ ላንተ የምሰጥህ


አምላክ ሆይ ውለታህ እጅግ የበዛ ነው

ቤት አልሰራልህም ዙፋንህ ሰማይ ነው

ብር ወርቁ ያንተ ነው ምን እሰጥሃለሁ

ብቻ በአንደበቴ ተመስገን እላለሁ


እንደዳዊት ልዝለል ልዘምር ልጨፍር

አዳኝነትህን ገድልህን ልናገር

ጌታ ለውለታህ የለም የምከፍልህ

የኔ ታሪክ ድርሻ አንተን ማሞገስ ነው


ሐጥያት መስራት ትቼ ወዳንተ ብመለስ

በአለም ዙሪያ ሮጬ ወንጌልን ባዳርስ

ሰማይና ምድርን እንደ ንስር ባስስ

ጌታ ውለታህን አልችልም ልመልስ


Report Page