ምንም ብሆን - Sofia Shibabaw
Sofia Shibabaw | Sema Belewየኔን ፡ ጠያፉን ፡ ሕይወት
ውበትን ፡ ጨምሮበት
ሳላውቅ ፡ ባለማመን ፡ ስላደረኩት
አገኘሁ ፡ ምህረት (፪x)
ምንም ፡ ብሆን ፡ ጌታ ፡ ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ደሙ ፡ አሳምሮኝ
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከሰይጣን ፡ አፍ ፡ አውጥቶኛል
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከጉድ ፡ ከእፍረት ፡ አውጥቶኛል
በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን
አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ጎን (፪x)
ከቤቴ ፡ እንዳትገባ ፡ ብዬው ፡ የነበረው
በፍቅር ፡ መጣና ፡ ታሪኬን ፡ ቀየረው
አንድ ፡ ሁሉት ፡ ብሎ ፡ የሚቆጠር ፡ ጽድቄ
ምን ፡ ነበረኝና ፡ ከአብ ፡ፊት: ርቄ
በመካከል ፡ ገብቶ ፡ ጠበቃዬ ፡ ዋሴ
ደጉ ፡ ኢየሱሴ
ግርማን ፡ ከሚያሳጣኝ ፡ ሥራዬ ፡ ተሽሮ
ዛሬስ ፡ እገኛለሁ ፡ ቆሻሻዬን ፡ ሁሉ
ደሙ ፡ አሳምሮ
ቃሉ ፡ አሳምሮ
መንፈሱ ፡ አሳምሮ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ደሙ ፡ አሳምሮኝ
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከሰይጣን ፡ አፍ ፡ አውጥቶኛል
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከጉድ ፡ ከእፍረት ፡ አውጥቶኛል
በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን
አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብሆን (፪x)
የት ፡ አለኝ ፡ በጐነት ፡ የለኝ ፡ መልካምነት
ልናገር ፡ በድፍረት ፡ እንዲህ ፡ ነው ፡ ምልበት
የተላለፈብኝ ፡ የመርገም ፡ ሀረጌ
አየሁት ፡ በክንዱ ፡ ሲሰብረው ፡ ጌታዬ
እኔነቴን ፡ አልፎ ፡ ለመጣው ፡ ሊፍክር
ኧረ ፡ እንዴት ፡ አልዘምር
ምንም ፡ ብሆን ፡ ይህን ፡ አረገልኝ ፡ ጌታ
እስቲ ፡ ላመስግነው ፡ ከውስጥ ፡ ከመንፈሴ
ተሰብሯል ፡ ቀምበሬ
የድል ፡ ቀን ፡ ነው ፡ ዛሬ
ያክብረው ፡ ከንፈሬ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ጌታዬ ምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ቃሉ አሳምሮኝ
ምንም ፡ ብሆን ፡ ደሙ ፡ አሳምሮኝ
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከሰይጣን ፡ አፍ ፡ አውጥቶኛል
ደጉ ፡ ኢየሱስ ፡ ደርሶልኛል
ከጉድ ፡ ከእፍረት ፡ አውጥቶኛል
በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን
አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብሆን (፪x)
በቃ ፡ ልጅ ፡ ነኝ ፡ እኔ
ተሰብሯል ፡ ኩነኔ
ተጥሏል ፡ ከሳሼ
ማጥ ፡ ውስጥ ፡ አልገኝም ፡ ዳግም ፡ ተመልሼ
በምህረቱ ፡ ባለጠጋ
ኢየሱስ ፡ ወደ ፡ እኔ ፡ ተጠጋ
ምንም ፡ ብሆን ፣ ምንም ፡ ብሆን
አልጣለኝም ፡ ጌታ ፡ አለሁ ፡ በእርሱ ፡ ብሆን (፪x)