usd የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን

usd የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን

Walia Tender

የተለያየ ዓይነትና ደረጃ ያላቸው የዕጣን ምርቶች ሽያጭ የወጣ የጨረታማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር ኢግስኮ- ኢምዘደውአ/ ሸ01 ሐ/2013

በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ምርጥ ዘርና የደን ውጤቶችአቅርቦት ዘርፍ አዳማ፣ ቻግኒ፣ አሶሳ እና ሽሬ ቅ/ጽ/ቤቶች የሚገኙ የተለያየ ዓይነትናደረጃ ያላቸው ብዛት 2353 ኩንታል የዕጣን ምርቶች ባሉበት ሁኔታ በጨረታአወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡

ስለሆነም በዘርፉ የተሰማራችሁና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉሁሉ በጨረታው መሳተፍ የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ፤ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር፤ የተጨማሪ እሴትታክስ ምዝገባ የምስክርነት ወረቀት፤ የንግድ ምዝገባ የምስክርነት ወረቀት፤ በጨረታለመሳተፍ የሚሰጥ የምስክርነት ወረቀት (ክሊራንስ) ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  2. የጨረታውን ሰነድ ዘወትር በሥራ ሰዓት (ከ11፡00 ሰዓት በፊት) በዋናው መ/ቤትየግብርና ምርት ማሳደጊያዎች አቅርቦት ዘርፍ ህንፃ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 4 የማይመለስ ብር 100.00 ( አንድ መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡፡
  3. ተጫራቾች ለጨረታው ዋስትና ማስከበሪያ የጠቅላላ ዋጋውን ከ20% ያላነሰCPO በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን የኢትዮጵያ ምርጥ ዘርና የደንውጤቶች ኦቅርቦት ዘርፍ ስም ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል የጨረታው ዋጋ ለ60 ቀናትየፀና መሆን ይኖርበታል፡፡
  4. ማንኛውም ተጫራች የዋጋ ማቅረቢያ ቅጽ የሚጠይቀውን በሙሉ አሟልቶ ማቅረብይጠበቅበታል የተለያየ ዓይነት ደረጃ ያላቸው የዕጣን ምርቶች ተጫራቹ በሚሰጠውዋጋ ላይ 15% ተጨማሪ እሴት ታክስ ያጨመራል፡፡
  5. ጨረታው ነሐሴ 15 ቀን 2012 ዓ. ከቀኑ በ8 ፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀንከቀኑ 8 ፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዘርፉመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
  6. ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ላይ ከቀረበው ዝርዝር ምርቶች ውስጥ በሙሉ ወይምበከፊል መጫረት ይችላሉ፡፡
  7. ማንኛውም ተጫራች በሌላ ተጫራች ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይቻልም፤
  8. ዘርፉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝመብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ስልክ ቁጥር 011 663 21 93/ ፋክስ 011 663 08 92

አዲስ አበባ ኢትዮጵያ

በኢትዮጵያ የግብርና ሥራዎች ኮርፖሬሽን

የኢትዮጵያ ምርጥ ዘርና ደን ውጤቶች አቅርቦት ዘርፍ


Posted:አዲስ ዘመን ነሀሴ 5 ቀን 2012
Deadline: August 21, 2020


© walia tender

Report Page