Sport

Sport

ETHIO ሪፖርተር

የአውሮፓ ቻምፒየንስ ሊግ ሁለተኛ ዙር የምድብ ጨዋታዎች ትናንት ምሽት በተለያዩ ከተሞች ተካሄደዋል፡፡

በምድብ አንድ ከሜዳው ውጭ ከሎኮሞቲቭ ሞስኮ የተጫወተው ባየር ሙኒክ 2 ለ 1 ሲያሸንፍ አትሌቲኮ ማድሪድ ሳልዝበርግን 3 ለ 2 አሸንፏል፡፡

በምድብ ሁለት የተደረጉ ጨዋታዎች ደግሞ በአቻ ውጤት ተጠናቀዋል፡፡

ሻካታር ከኢንተር ሚላን ያለምንም ጎል እንዲሁም ቦሩሲያ ሞንቼግላድባህ ከሪያል ማድሪድ 2 አቻ ጨዋታቸውን አጠናቀዋል፡፡

በምድብ ሶስት ፖርቶ ኦሊምፒያኮስን 2 ለ 0 እንዲሁም ማንቼስተር ሲቲ ከሜዳው ውጭ ማርሴይን 3 ለ 0 ማሸነፍ ችለዋል፡፡

በምድብ አራት ደግሞ አታላንታ ከአያክስ ያደረጉት ጨዋታ ሁለት አቻ በሆነ ውጤት ተጠናቋል፡፡

በሜዳው ሚዲቲላንድን ያስተናገደው ሊቨርፑል ደግሞ 2 ለ 0 አሸንፏል፡፡

ከምድብ አምስት እስከ ስምንት በሚገኙ ቡድኖች መካከል የሚደረጉ ጨዋታዎች ደግሞ ዛሬ ምሽት ይደረጋሉ፡፡

ዛሬ የሚደረጉ የአውሮፓ ሻምፕዮንስ ሊግ መርሃ ግብሮች፦ 

     ⏰ 2:55

ባሳክሼር Vs ፒኤስ ጂ

ኬራስኖዳር Vs ቼልሲ 

     ⏰ 5:00

ጁቬንቱስ Vs ባርሴሎና

ማን ዩናይትድ Vs RB ሌፕዚሽ

ክለብ ብሩጅ Vs ላዚዮ

ዶርትሙንድ Vs ዜኒት 

ሴቪያ Vs ሬኔስ

ፈረንስቫሮስ Vs ዳይናሞ ኬቭ


Via: Elias

Report Page