sl tx pr fr ins ctr ን ስ ላፍቶ ክ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳ

sl tx pr fr ins ctr ን ስ ላፍቶ ክ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳ

Walia Tender

የግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር 001/2013

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር የ2013 ዓመት የ1ኛ ዙር ግዥ

አላቂ የፅህፈት መሳሪያ ዕቃ እና
የደንብ ልብስ
የጽዳት ዕቃ
እርሻ መሳሪያዎች
የህትመት
የወንበር ጥገና
የፎቶ ኮፒ ጥገና
የምግብና መጠጥ 

በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል ስለሆነም

ተጫራቾች ፡-

  1. የዘመኑ ግብር የከፈሉ በዘርፉ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
  2. በመንግስት ግዥ እና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ የተመዘገቡበትን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  3.  የጨረታ ማስከበሪያ ለሎት1 (አላቂ የጽህፈት መሳሪያ) ብር 5000 ሎት3 (የደንብ ልብስ) ብር 5000 ሎት2 (የጽዳት ዕቃ) ብር 5000 ለሎት4( የእርሻ መሳሪያ) ብር 3000 የህትመት ብር 2000 የጠረጴዛ የሼልፍ ጥገና ብር 2000 የፎቶ ኮፒ ብር 2000 የምግብና የመጠጥ ብር 2000 የጨረታ ሰነድ ሲያስገቡ ሲፒኦ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
  4. የተጠቀሰው የጨረታ ማስከበሪያ ብር ለተሽናፊው ድርጅት ወዲያወኑ ተመላሽ ሲሆን አሸናፊው ድርጅት ደግሞ የወል ማስከበሪያ የወሉን 10% አስይዘው እንደተፈራረሙ በጨረታው ለጨረታ ማስያዣነት የተያዘው ብር ወዲያውኑ ይመለስላቸዋል፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘው ሰነድ ለእያንዳንዱ ሰነድ በማይመለስ ብር 50/ሀምሳ ብር/ በመከፈል ይህ ጨረታ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10(ኣስር) የስራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ፋ/ኢ/ል/ጽ/ ቤት ምድር ላይ ቢሮ ቁጥር 1 የጨረታውን ሰነድ መግዛት ይችላሉ።
  6. ተጫራቾች ከሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሰነድ ላይ ስማቸውን ፊርማቸውን አድራሻቸውን እና የድርጅታቸውን ማህተም ማድረግ አለባቸው።
  7.  ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ከ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 (ሶስት ሰዓት) ላይ ታሽጎ 4፡00 (አራት ሰዓት) ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ግ/ን/አ/ደ/የስ/ ሂደት ቢሮ ቁጥር 1 ላይ ይከፈታል።
  8. መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  9. በጥቃቅን እና አነስተኛ የድጋፍ ደብዳቤ ሲያመጡ በጽ/ቤቱ ሀላፊ የተፈረመ መሆን አለበት ይህ ካልሆነ ከጨረታው ውድቅ ይደረጋሉ።

ለተጨማሪ መረጃ ስልክ ቁጥሮች ደውለው ይጠይቁ 011-4-70-55-65/011-4-67-23-99/

አድራሻ ጎፋ ገብርኤል 100 ሜትር ገባ ብሎ ፀሀይ ፔንሲዮን አጠገብ ሶፊያ ሞል ገባ ብሎ

ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ በሚያስገቡበት ወቅት የዕቃ ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ያቀረቡት ናሙናም በ6 ወር ውስጥ ካልወሰዱት ለመንግስት ገቢ ይሆናል::

በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ የወረዳ 06 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት

__________________

Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 7፣2013

Deadline:11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00

__________________
© walia tender

Report Page