sl tx ot በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስ

sl tx ot በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስ

Walia Tender

የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ

በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር ጽ/ቤት የ2013 ዓ.ም ለ1ኛ ዙር

አላቂ እና ቋሚ የቢሮ እቃዎች (stationary)
የጽዳት እቃዎች ፤
የደንብ ልብስ ግዥ ፤የደንብ ልብስ ስፌት ፤
ልዩ ልዩ መሳሪያዎችንና እቃዎችን 

በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ አቅራቢ ድርጅቶች መወዳደር የምትችሉ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

  1. ተጫራቾች የተዘመኑን የመንግስት ግብር የ2012 ዓ.ም የከፈሉና የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸው መሆን አለባቸው::
  2.  የቫት ተመዝጋቢና ህጋዊ የማቅረቢያ ሰርተፍኬት ያላቸው መሆናቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ማቅረብ አለባቸው::
  3. ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ10 ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል የጨረታ ሰነድ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 ፋይናንስ ጽ/ቤት ቢሮ መግዛት ይችላሉ፡፡
  4.  ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ ክፍል 6 ውስጥ የተገለጹትን እቃዎች ዝርዝር ዋጋቸውን ስታሽገ ኤንቨሎፕ ቂ/ክ/ከተማ ወረዳ 4 ፋይናንስ ጽ/ቤት ለዚህ የተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው::
  5. የጨረታ ማስከበሪያ ብር 6000.00 (ስድስት ሺ) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  6. ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት እቃ ናሙና ለሚያስፈልጋቸው እቃዎች ናሙና የማስገባት ግዴታ አለባቸው::
  7.  አሸናፊ ድርጅቶች በናሙናው መሰረት ደረጃውን የጠበቀ እቃ የማስገባት ግዴታ አለባቸው፡፡
  8. ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 ታሽጎ በዚያኑ ቀን 3፡30 በፋ/ጽ/ቤት ይከፈታል፡፡ 11ኛው ቀን በአል ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ጨረታው ይከፈታል፡፡
  9. መቅረብ ያለባቸው መረጃዎች ኦሪጅናልና ኮፒ ሲሆን ሁለቱም ለየብቻቸው መታሸግ አለባቸው :: ነገር ግን ጨረታው ሲከፈት የሚከፈተው ኮፒው በመሆኑ ሲፒኦ (CPO) እና ሌሎች አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎች በሙሉ ኮፒው ውስጥ መደረግ አለባቸው፡፡ በሁለቱም ኤንቨሎፕ ላይ የድርጅቱ ማህተም መደረግ አለበት፡፡
  10. ተጫራቾች ያሸነፉሰትን እቃ ዋጋ ድምር 10% የውል ማስከበርያ ከውል በፊት ማስያዝ አለባቸው :: የእያንዳንዱ እቃ ዋጋ ቫትን ያካተተ (ቫት ተጨምሮበት) መቅረብ አለበት፡፡ ይህንን ያላደረጉ ተጫራቾች ከጨረታው ውጭ ይሆናሉ፡፡
  11. ተጫራቾች ለሚኖራቸው ጥያቄዎች ወይንም መረጃ ማግኘት ለሚፈልጉ ስልክ ቀጥር 0118883069  መጠቀም ይችላሉ፡፡

አድራሻችን ከዲናፖል ሆተል ጀርባ ቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 04 አስተዳደር ጽ/ቤት

ማሳሰቢያ፡- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

በቂርቆስ ክፍስ ከተማ የወረዳ 4 አስተዳደር ጽ/ቤት

__________________

Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 9፣2013

Deadline:በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 3፡00 

__________________
© walia tender


Report Page