sl ctr tx lb vi የደብረዘይት ግብርና ምርምር ማዕከል

sl ctr tx lb vi የደብረዘይት ግብርና ምርምር ማዕከል

Walia Tender

የጨረታ ማስታወቂያ

ቁጥር 01/2012

በኢትዮጵያ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የደብረዘይት ግብርና ምርምር ማዕከል ከዚህ በታች የተጠቀሰውን አላቂና ቋሚ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።

ሎት 1 የእንሰሳት መኖ
ሎት 2. የሠራተኞች ደንብ ልብስ
ሎት 3. አላቂ የጽህፈት መሣሪያዎች
ሎት 4. አላቂ የጽዳት ዕቃዎች እና አላቂ የመስክ መገልገያ ቁሳቁሶች
ሎት 5. አነስተኛ የእጅ መገልገያ እና የእርሻ መሣሪያዎች
ሎት 6. የግብርና ግብዓቶች (ፀረ-አረም እና ፀረ-ተባይ መድኃኒቶች)
ሎት 7. የላቦራቶሪ ኬሚካል እና የላቦራቶሪ መሣሪያዎች
ሎት 8. የመኪና እና የትራክተር ጎማዎች

በዚህ መሠረት ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሰነድ ከደብረ ዘይት ግብርና ምርምር ማዕከል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር) በመክፈል መግዛት ይችላሉ።

  • ተጫራቾች በመስኩ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልጽ የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት፣የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ጨረታ ለመካፈል የሚያስችል የድጋፍ ደብዳቤ፣የንግድ ምዝገባ ሰርተፍኬት/በአቅራቢነት ዌብ ሳይት የተመዘገቡበት ኮፒ እና ለተጫረቱበት ዕቃ ናሙና በማቅረብ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማዕከሉ በተዘጋጀው ሳጥን እስከ መስከረም 28 ቀን 2013 ዓ.ም 4:00 ሰዓት ድረስ ማስገባት አለባቸው።
  • ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ብር 3000.00 (ሶስት ሺህ) በሲፒኦ ወይም በተመሳሳይ ማስያዝ ይጠበቅባቸዋል።
  • የጨረታ ሳጥኑ መስከረም 28 ቀን 2013 ዓ.ም በ4:00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ4፡30 ሰዓት በማዕከሉ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል።
  • ማዕከሉ የተሻለ መንገድ ካገኘ በሙሉም ሆነ በከፊል በጨረታው አይገደድም

በተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር፡-0114339472/0912229367

የደብረ ዘይት ግብርና ምርምር ማዕከል  

__________________

Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 7፣2013

Deadline:መስከረም 28 ቀን 2013

__________________
© walia tender

Report Page