ot አንፕካን - ኢትዮጵያ

ot አንፕካን - ኢትዮጵያ


Walia Tender

የሚኒ ሚዲያ መሣሪያዎች ግዥ ጨረታ

አፍሪካን ኔትወርክ ፎር ዘ ፕሪቬንሽን ኤንድ ፕሮቴክሽን አጌንስት ቻይልድ አቢዩዝ አንድ ኔግሌክት /አንፕካን - ኢትዮጵያ መንግሥታን ያልሆነ ሀገር በቀል የሲቪል ማህበረሰብ ድርጅት ሲሆን ከፕላን ኢንተርናሽናል ኢትዮጵያ ጋር በመተባበር በአማራ ክልል አዊ ዞን ውስጥ ለሚገኙ ትምህርት ቤቶች ክበባት ለሚያካሂደው የድጋፍ ሥራ የሚኒ ሚዲያ መሣሪያዎችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል::

ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ፡

  1. በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
  2. ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ሥራ መሠራቱንና በመልካም ሁኔታ መፈጸሙን ማስረጃ ማቅረብ የሚችል::
  3. የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ 2% በባንክ በተመሰከረለት ቼክ (CPO) ከጨረታ፣ስነድ ጋር አያይዞ ማቅረብ የሚችል፣
  4. ተጫራቾች የግዥውን ዝርዝር ሰነድ አዲስ አበባ ጉርድ ሾላ ወረዳ 9 አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንፃ ጐን ከሚገኘው ከድርጅቱ ዋና ጽ/ቤት መውሰድ ይችላሉ::
  5. የሚፈለጉትን ቁሳቁሶች ወዲያውኑ ማስረከብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል::
  6. ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በገዙት ሰነድ ላይ ባለው የዋጋ ማቅረቢያ ቦታ በመሙላት ዋናውንና ኮፒውን በተለያየ ፖስታ በማድረግና ሁለቱን ፖስታዎች በአንድነት በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ አድርገው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10 ተከታታይ ቀናት ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ::
  7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ በ4፡00 ታሽጎ በ4፡30 ሰዓት በአንፕካን ዋና መ/ቤት ይከፈታል፡
  8. ተጨራቾች የተጨማሪ እእሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለባቸው
  9. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  10. ለተጨማሪ መረጃ ከዚህ በታች በተገለጸው አድራሻ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ::

አንፕካን ኢትዮጵያ

የካ ክፍለ ከተማ ቀበሌ 9 አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ሕንፃ ጎን 4ኛ ፎቅ

ስልክ 0115505202

አንፕካን - ኢትዮጵያ

__________________

Posted:ሪፖርተር መስከረም 10፣2013

Deadline:በ11ኛው ቀን በ4፡00

__________________
© walia tender


Report Page