Hope
Anonymousየሱዳን ጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ የስልጣን መልቀቂያ ለማስገባት የደረሱበትን የውሳኔ ሀሳብ ማጠፋቸው/ማንሳታቸው ተሰምቷል።
ከሳዑዲ ጋዜጣ ላይ እንዳነበብነው ጠቅላይ ሚኒስትሩ ስልጣናቸውን ለመልቀቅ የደረሱበትን የውሳኔ ሀሳብ አንስተውታል።
ጠቅላይ ሚኒስትር አብደላ ሀምዶክ ሀሳባቸውን ያነሱት ከሌ/ጄኔራል አብዱል ፈታህ አል ቡርሃን ጋር ውይይት ካደረጉ በኃላ መሆኑን ጋዜጣው ምንጮቹ እንደነገሩት አስነብቧል።
በሌላ በኩል የአሜሪካ 🇺🇸 አፍሪካ ጉዳዮች ቢሮ ዛሬ ከጠ/ሚ አብደላ ሀምዶክ እና ከአል ቡርሃን ጋር ጠቃሚ ውይይት ለማድረግ እድል በማግኘቱ አመስግኖ " አሜሪካ የሱዳን መሪዎች የሱዳንን ህዝብ የነጻነት ፣ የሰላም እና የፍትህ ምኞት ለማሳካት አስፈላጊውን እርምጃ እንዲወስዱ ማበረታቷን ቀጥላለች ሲል " ገልጿል።
ትላንት ምሽት የሱዳኑ ጠ/ሚ አብደላ ሃምዶክ በሰዓታት ውስጥ ስልጣን ለመልቀቅ እንዳሰቡ ለፖለቲከኞች ቡድን መናገራቸውን ሮይተርስ ለሃምዶክ ቅርብ ከሆኑ 2 ምንጮች መስማቱን መዘገቡ ይታወሳል።
https://t.me/sketethiopia