#ETH
ህዝቡ ለሀገር ሰላምና አንድነት በጋራ ሊቆም እንደሚገባ የሆሮጉድሩ ወለጋ ዞን አባገዳዎች አስገነዘቡ ።
በዞኑ የኦዳ ቡሉቅ ኢሬቻ በዓል ትናንት ተከብሯል ።
የኦዳ ቡሉቅ አባ ገዳ ደቻሣ ወዳጆ በስነ ስርዓቱ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት ኢሬቻ የአንድነት፣ የሠላም፣የፍቅርና የወንድማማችነት ተምሳሌት ነው ።
በዓሉ ዘርና ሃይማኖት ሳይለይ ሁሉን በማሳተፍ የሚከበር መሆኑን ተናግረዋል ።
ህዝቡም በዓሉን ሲያከብር በሀገሪቱ ሰላምና አንድነት እንዲሰፍን ፈጣሪውን በመለመንና ለተግባራዊነቱም በጋራ ቃል በመግባት ሊሆን እንደሚገባ አስገንዝበዋል ።
“ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አቢይ አህመድ የዓለም የኖቤል ሠላም ተሸላሚ በሆኑበት ወቅት በዓሉ መከበሩ ከወትሮው ልዩ ያደርገዋል” ብለዋል።
“በጠቅላይ ሚኒስተሩ የተገኘውን የሰላም ስኬት በማጠናከር ሀገራዊ ለውጡን ማስቀጠል ይገባል”ሲሉም መልዕክት አስተላልፈዋል ።
በአባገዳዎች ምርቃት የተጀመረው የበዓሉ አከባበር ስነ ስርዓት በሰላም ተጠናቋል ።
VIA ENA