#ETH

#ETH


በ2011 በጀት አመት በተለያዩ ክልሎች በተፈጠሩ ግጭቶች ተሳትፈዋል በተባሉ 1 ሺህ 323 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ፡፡

በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ 1 ሺህ 229 ሰዎች ህይዎት ያለፈ ሲሆን በ1 ሺህ 393 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ19 ሰዎች ላይ የግድያ ሙከራ መደረጉን በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁ ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ ገልፀዋል፡፡

በግጭቶቹ ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዜጎች ንብረት የወደመ ሲሆን፤ 1.2 ሚሊዮን ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸውና ከአካባቢያቸው ተፈናቅለዋል፡፡

ከተከሳሾቹ መካከል 645 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ሲሆን 667 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎች ደግሞ በቁጥጥር ስር አልዋሉም፡፡

የ10 ተጠርጣሪዎች ክስም በምህረት መነሳቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ፍቃዱ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረግ እንቅስቃሴ ዙሪያ የሚስተዋለው ክፍተት አስመልክቶ መፍትሔ ያሉትን ሀሳብ ሲጠቁሙ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከፍትህ አካላት ጎን በመቆምና ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ በመስጠት በኩል በጉዳዩ ላይ በባለቤትነት ስሜት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽእኖት ሰጥተው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በሌላ በኩል በአማራ ክልል በጃዊ ወረዳና በመተክል ዞን፤ በጎንደርና አካባቢው በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ፤ በሰሜን ሸዋ አስተዳደር እንዲሁም በቤንሻጉል ጉምዝ ክልል ከማሻ ዞን ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎችና የዚሁ ዞን አጎራባች በሆነው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞን በተለያዩ ቀበሌዎች ላይ በተፈፀመ ብጥብጥና ሁከት በአሶሳ ዞን አራት ወረዳዎች ውስጥ በኦሮሚያና በበርታ ብሄረሰብ መካከል በተፈጠረ ግጭት ተሳታፊ የነበሩ በአጠቃላይ 1647 ተጠርጣሪዎች ተለይተውና አስፈላጊው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ተሰባስበው እስካሁን ድረስ 185 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ የተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ሀላፊዉ ቀሪዎችን 1462 ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የማፈላለግ ስራም እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ አቃቢ ህግበ2011 በጀት አመት በተለያዩ ክልሎች በተፈጠሩ ግጭቶች ተሳትፈዋል በተባሉ 1 ሺህ 323 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ፡፡

በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ 1 ሺህ 229 ሰዎች ህይዎት ያለፈ ሲሆን በ1 ሺህ 393 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ19 ሰዎች ላይ የግድያ ሙከራ መደረጉን በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁ ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ ገልፀዋል፡፡

በግጭቶቹ ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዜጎች ንብረት የወደመ ሲሆን፤ 1.2 ሚሊዮን ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸውና ከአካባቢያቸው ተፈናቅለዋል፡፡

ከተከሳሾቹ መካከል 645 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ሲሆን 667 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎች ደግሞ በቁጥጥር ስር አልዋሉም፡፡

የ10 ተጠርጣሪዎች ክስም በምህረት መነሳቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ፍቃዱ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረግ እንቅስቃሴ ዙሪያ የሚስተዋለው ክፍተት አስመልክቶ መፍትሔ ያሉትን ሀሳብ ሲጠቁሙ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከፍትህ አካላት ጎን በመቆምና ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ በመስጠት በኩል በጉዳዩ ላይ በባለቤትነት ስሜት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽእኖት ሰጥተው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በሌላ በኩል በአማራ ክልል በጃዊ ወረዳና በመተክል ዞን፤ በጎንደርና አካባቢው በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ፤ በሰሜን ሸዋ አስተዳደር እንዲሁም በቤንሻጉል ጉምዝ ክልል ከማሻ ዞን ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎችና የዚሁ ዞን አጎራባች በሆነው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞን በተለያዩ ቀበሌዎች ላይ በተፈፀመ ብጥብጥና ሁከት በአሶሳ ዞን አራት ወረዳዎች ውስጥ በኦሮሚያና በበርታ ብሄረሰብ መካከል በተፈጠረ ግጭት ተሳታፊ የነበሩ በአጠቃላይ 1647 ተጠርጣሪዎች ተለይተውና አስፈላጊው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ተሰባስበው እስካሁን ድረስ 185 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ የተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ሀላፊዉ ቀሪዎችን 1462 ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የማፈላለግ ስራም እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ አቃቢ ህግበ2011 በጀት አመት በተለያዩ ክልሎች በተፈጠሩ ግጭቶች ተሳትፈዋል በተባሉ 1 ሺህ 323 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ አስታወቀ፡፡

በተፈጠረው ሁከትና ብጥብጥ 1 ሺህ 229 ሰዎች ህይዎት ያለፈ ሲሆን በ1 ሺህ 393 ሰዎች ላይ ደግሞ ቀላልና ከባድ የአካል ጉዳት ሲደርስ በ19 ሰዎች ላይ የግድያ ሙከራ መደረጉን በጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተደራጁ ድንበር ተሸጋሪ ወንጀሎች ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ፍቃዱ ፀጋ ገልፀዋል፡፡

በግጭቶቹ ከ2.2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚገመት የዜጎች ንብረት የወደመ ሲሆን፤ 1.2 ሚሊዮን ዜጎች ከመኖሪያ ቤታቸውና ከአካባቢያቸው ተፈናቅለዋል፡፡

ከተከሳሾቹ መካከል 645 ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ውለው ጉዳያቸው እየታየ ሲሆን 667 የሚሆኑ ተጠርጣሪዎች ደግሞ በቁጥጥር ስር አልዋሉም፡፡

የ10 ተጠርጣሪዎች ክስም በምህረት መነሳቱን ዳይሬክተሩ አክለዋል፡፡

በመጨረሻም አቶ ፍቃዱ ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር ለማዋል በሚደረግ እንቅስቃሴ ዙሪያ የሚስተዋለው ክፍተት አስመልክቶ መፍትሔ ያሉትን ሀሳብ ሲጠቁሙ ይህንን ችግር ለመቅረፍ ህብረተሰቡና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ከፍትህ አካላት ጎን በመቆምና ተጠርጣሪዎችን አሳልፎ በመስጠት በኩል በጉዳዩ ላይ በባለቤትነት ስሜት ሊሰሩ እንደሚገባ አጽእኖት ሰጥተው መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በሌላ በኩል በአማራ ክልል በጃዊ ወረዳና በመተክል ዞን፤ በጎንደርና አካባቢው በተፈጠረ ሁከትና ብጥብጥ፤ በሰሜን ሸዋ አስተዳደር እንዲሁም በቤንሻጉል ጉምዝ ክልል ከማሻ ዞን ውስጥ በሚገኙ የተለያዩ ወረዳዎችና ቀበሌዎችና የዚሁ ዞን አጎራባች በሆነው በኦሮሚያ ክልል ምስራቅና ምዕራብ ወለጋ ዞን በተለያዩ ቀበሌዎች ላይ በተፈፀመ ብጥብጥና ሁከት በአሶሳ ዞን አራት ወረዳዎች ውስጥ በኦሮሚያና በበርታ ብሄረሰብ መካከል በተፈጠረ ግጭት ተሳታፊ የነበሩ በአጠቃላይ 1647 ተጠርጣሪዎች ተለይተውና አስፈላጊው የሰውና የሰነድ ማስረጃዎች ተሰባስበው እስካሁን ድረስ 185 ተጠርጣሪዎችን በቁጥጥር ስር የማዋሉ ስራ የተከናወነ መሆኑን የጠቀሱት ሀላፊዉ ቀሪዎችን 1462 ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የማፈላለግ ስራም እየተሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡

ጠቅላይ አቃቢ ህግ

Report Page