Covid-19

Covid-19

ATC

በሽታው የጋራችን፤ ክትባቱ የግላችን?

===============

የሐብታም ሀገራት መንግስታት 8.8 ቢሊዮን ፍሬ ክትባት ለመግዛት የሚያስችላቸውን ስምምነት እያከናወኑ ሲሆን ይህም ደሀ ሀገራት ክትባቶቹን ቢያንስ እስከ አውሮፓውያኑ 2024 ድረስ እንዳያገኙ የሚያደርግ መሆኑ ተነግሯል፡፡

እስካሁን በሙከራ እና ሌሎች ሂደቶች ውስጥ እያለፉ ካሉት 320 በላይ ክትባቶች ውስጥ አንዳቸውም ጥቅም ላይ እንዲውሉ ፍቃድ ያልተሰጣቸው ቢሆንም እስካሁን ድረስ የሐብታም ሀገራት መንግስታት 3.73 ቢሊዮን ፍሬዎችን ለመግዛት የሚያስችል ስምምነት ከመድሃኒት አምራች ኩባንያዎች ጋራ ገብተዋል፤ 5 ቢሊዮን ፍሬ ለመግዛት የሚያስችሉት ስምምነቶችም በቅርብ የሚደረሱ ይሆናሉ፡፡

የመድሃኒት አምራቾች በአሁኑ ሰዓት ያላቸው አቅም እነዚህ እጩ ክትባቶችን በማምረት ብቻ የተወሰነ ነው፤ ይህ ማለት ክትባቶችን ወደተቀረው የዓለማችን ህዝብ በማድረስ ከወረርሺኙ ለመታደግ ሦስት አልያም አራት ዓመታት ሚያስፈልጉ ይሆናል፡፡ በነዚህ ወቅቶች የደሃ ሀገራት ዜጎች በክትባት አማካኝነት ከወረርሺኙ ከመጠበቃቸው አስቀድሞ ሐብታም ሀገራት ጠቅላላው ህዝባቸውን በተደጋጋሚ ክትባት ለማስከተብ የሚችሉ ይሆናል፡፡

ቅድም ስምምነት


የዓለም ጤና ድርጅት ኮቫክስ (Covax) በተባለው እቅዱ አማካኝነት ፈራሚ ሀገራት ስኬታማ የሆኑትን ክትባቶች በእኩል መጠን እንዲካፈሉ ለማድረግ እየሰራ ነው፡፡ በዚህም ክትባቶቹን በመጀመሪያ ለጤና እና የደህንነት ባለሙያዎች፤ በመቀጠልም ቢያንስ 20 በመቶ ለሚደርሰው የሀገራቱ ህዝብ ለማድረስ ለማድረስ አስቧል፡፡ ታድያ ሐብታም ሀገራቱ ለዚህ እቅድ ድጋፍ ሲያደርጉ ቢቆዩም አሁን ግን ከመድሃኒት አምራቾቹ ጋራ ከጥታ ስምምነት ውስጥ ገብተዋል፡፡ ይህም በኮቫክስ አማካኝነት በእኩሌታ ይከፋፈል የነበረውን ክትባት ለራሳቸው ብቻ ያስቀረ ነው፡፡

ኢትዮጵያን ለምሳሌ ብናነሳ በኮቫክ አማካኝነት 20 በመቶ የሚሆነው ህዝቧ ክትባቱን ያገኝ የነበረ ቢሆንም ምንም አይነት የጎንዮሽ ስመምነት ውስጥ ሰባለመግባቷ ምክንያት እንደ እንግሊዝ ያሉት ሀገራት ህዝባቸውን ሙሉ ለሙሉ ከበሽታው ሲጠበቁ አብዛኛው ኢትዮጵያዊ ግን ለዓመታት ክትባቱን ሳያገኝ ይቀራል፡፡

ሌላኛው በክትባት ዙርያ ያለ ችግር በቅዝቃዜ ስፍራ መቀመጥ ላለባቸው ክትባቶችን እንዲሁም በከፍተኛ ሙቀት መቀመጥ የሚገባቸው ቁሳቁሶችን ለማስቀመጫ የሚሆን በቂ መሰረተ ልማረትና አቅም ማጣት ነው፡፡ ጆንሰን እና ጆንሰን ድርጅት በቅድሚያ የሚያመርታቸው በመቶ ሚሊዮኖች የሚቆተሩ በመጠነኛ የማቀዝቀዣ ቅዝቃዜ ውስጥ ያለምንም ችግር ለብዙ ወራት መቀመጥ የሚችሉ እጩ ክትባቶች ይህን የማቀዝቀዣ ችግር ሊያቃልሉ የሚችሉ ናቸው፤ ሆኖም እነዚህ ክትባቶችንም አሜሪካን፣ ካናዳ፣ እንግሊዝ እና የአውሮፓ ሕብረት አስቀድመው በገፍ ገዝተዋቸዋል፡፡

ኮቫክስ እስካሁን ድረስ 250 ሚሊዮን ህዝብን መከተብ የሚችል ክትባት መግዛቱ ታውቋል፡፡ ይህ ግን ቀድሞ ሊሸፍነው አስቦት ከነበረው 1.14 ቢሊዮን ህዝብ አንፃር እዚህ ግባ የሚባል አይደለም፡፡ ቸርነት ካሳዩት ጥቂት ሐብታም ሀገራት መካከል የሆነችው አውስትራሊያ ለ25 ሚሊዮን ህዝቧ ለመግዛት ከተስማማችው 80 ሚሊዮን ክትባቶች ውስጥ ለደሀ ሀገራትም ለማካፈል ፍቃደኝነቷን ገልፃለች፤ ምንም እንኳን የምታካፍለው በህዝብ ብዛት ሚጢጢ ለሚባሉት እንደ ቫኑአቱ እና ፊጂ ላሉ ጎረቤት ሀገራት ቢሆንም፡፡

ከዚህ ቀደም ከጤና ባለሙያዎች ሰፈር ሀገራት ግብዓቶቻቸውን ለራሳቸው በመሰብሰብ እና ወደውጭ የሚላኩት ላይም ከፍተኛ ቁጥጥር በማድረግ የሚከናወን የክትባት ብሔረተኝነትን የኮቪድ-19 ወረርሺኝን ይበልጥ ላልተፈለገ ጊዜ በዓለም ላይ እንዲቆይ ያደርግ ይሆናል የሚል ስጋታቸውን ሲያነሱ ነበር፡፡

ምንጭ፡ The Guardian

@amharictutorialclass

@amharictutorialclass

Report Page