car usd የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 

car usd የኢትዮጵያ መድን ድርጅት 

Walia Tender

የጨረታ ማስታወቂያ

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት አደጋ ደርሶባቸው ለደንበኞቹ ሙሉ የመድን ካሣ ከፍሎ የተረከባቸውን፡-

ቀረጥ የተከፈለባቸው ልዩ ልዩ ተሽከርካሪዎች፣
ልዩ ልዩ የተሽከርካሪ ውጫዊና የውስጥ አካላት፣
ሌሎች ልዩ ልዩ ብርታ ብረቶችን በጨረታ ለመሸጥ ይፈልጋል።

ማንኛውንም የስም ማዛወሪያ፣ ተጨማሪ የጉምሩክ ቀረጥ፣ ግብር፣ እሴት ታክስና ሌሎች ወጪዎች ቢኖሩ ከፍሎ በጨረታ ለመግዛት የሚፈልግ ሁሉ ቃሊቲ ክራውን ሆቴል በስተጀርባ በሚገኘው የድርጅቱ ሪከቨሪ ቴክኒክ ማዕከል በመገኘት ከመስከረም 13 ቀን 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ መስከረም 27 ቀን 2013 ዓ.ም ድረስ በመመልከትና የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ በማስያዝ መጫረት ይችላል።

ሀ/ የዕቃ ማስያዣ

የጨረታ መነሻ ዋጋ 20 በመቶ ሲሆን ዝቅተኛ የዕቃ ማስያዣ ብር 1000 ነው።

ለ/ የተሽከርካሪ ማስያዣ


ተጫራቾች የሚገዙበትን ዋጋ ከተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት ስመሙላት የጨረታውን ሠነድ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ከመስከረም 26 እና 27 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 10:00 ሰዓት ድረስ ለገሀር በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ለዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። ጨረታው መስከረም 28 ቀን 2013 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት በሪከቨሪ ቴክኒክ ማዕከል ይከፈታል።

በጨረታው ተሸናፊ ለሚሆኑ ተወዳዳሪዎች የጨረታ ማስከበሪያ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ከሁለት የሥራ ቀናት በኋላ ተመላሽ የሚደረግ ሲሆን፣ ለአሸናፊዎች ግን ሂሣቡ በገዙት ንብረት ላይ የሚታሰብ ሆኖ፣ የገዙትን ንብረት ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ የገዙትን ዋጋ አጠናቀው በ10 ቀናት ጊዜ ውስጥ ንብረቱን ሳይረከቡ ለጨረታ ተሳትፎ ያስያዙት ገንዘብ በመቀጫ መልክ ለድርጅቱ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል። ክፍያ ፈፅመው ንብረቶቹን በተገለፀው ጊዜ የማያነሱ ተጫራቶች የጥበቃ ወጪ በቀን ብር 150 (አንድ መቶ ሃምሳ ብር) ይከፍላሉ። ማንኛውም ተጫራች በጨረታ ያሸነፈውን ተሽከርካሪም ሆነ ቁሳቁስ በአለበት ሁኔታ በአንድ ጊዜ ማንሳት አለበት። ድርጅቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ ማብራሪያ በስልክ ቁጥር፡- 0011439-25-89 እና011439-25-45  መጠየቅ ይቻላል ።

የኢትዮጵያ መድን ድርጅት

__________________

Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 7፣2013

Deadline: መስከረም 27 ቀን 2013 

__________________
© walia tender

Report Page