Vi ins የአንዳቤት ወረዳ ገንዘብ ኢ

Vi ins የአንዳቤት ወረዳ ገንዘብ ኢ

Walia Tender

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

በደቡብ ጐንደር ዞን የአንዳቤት ወረዳ ገንዘብ ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት

  • ሎት 1 የመኪና ጎማ
  • ሎት 2 የመኪና መለዋለጫ እቃ እና
  • ሎት 3 የበር እና መስኮት ወይም የጠቅላላ ብረታ ብረት ብየዳ ስራ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

በመሆኑም በጨረታው ለመሣተፋ የተጋበዛችሁ በሙሉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ማሟላት ይጠበቅባችኋል፡፡

  1. በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
  2. የዘመኑን ግብር የከፈለ ለመሆኑ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
  3. የግዥ መጠኑ ከ200 ሺህ ብር በላይ ከሆነ ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ ወይም ቫት ከፋይነት መረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሣተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ያቀረቡትን ጠቅላላ የመወዳደሪያ ዋጋ ለእያንዳንዱ ሎት 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ/ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ/ደረሰኙን ፎቶ ኮፒ በማድረግ/ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማስያዝ ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 50 መግዛት አለባቸው፡፡
  7. ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን በ16ኛው ቀን 3፡30 ታሽጎ በዚሁ ቀን በ4፡00 ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በተገኙበት በአንዳቤት ወረዳ ገንዘብ ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት ግዥ ቢሮ ይከፈታል፡፡
  8. የጨረታው መዝጊያ ቀን ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሣብ ማሻሻያ ማድረግና ራሣቸውን ከጨረታው ማግለል አይችሉም፡፡
  9. የጨረታ አሸናፊ አሸናፊነቱ ከተገለፀበት ቀን ከ5 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 5 ተከታታይ ቀናት ያሸነፉትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ/ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ/ደረሰኙን ፎቶ ኮፒ በማድረግ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በማስያዝ ውል መውሰድ አለባቸው፡፡
  10. መስሪያ ቢቱ ከጨረታው 20 በመቶ የመቀነስና የመጨመር መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  11. መስሪያ ቤቱ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  12. የጨረታ አሸናፊ የሚለየው በጥቅል ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ያቀረቡ ሲሆን ሁሉም የእቃዎች ዋጋመሞላት አለባቸው፡፡
  13. ተጫራቾች በሚያቀርቡት የመወዳደሪያ ሰነድ ስማቸውን፣ ፊርማቸውንና ሙሉ አድራሻቸውን መግለጽ የድርጅቱ ማህተም መርገጥ ይኖርባቸዋል፡፡
  14. ለበለጠ መረጃ በአካል ቢሮ ቁጥር 3 በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር በ058547068 በመደወል መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የአንዳቤት ወረዳ ገንዘብ ኢኮኖሚ ልማት ጽ/ቤት


Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013

Deadline:በ16ኛው ቀን 3፡30


© walia tender

Report Page