Usd አፄ ናኦድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት
Walia Tenderግልጽ ዕቃ ሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2013
በአራዳ ክ/ከተማ አስተዳደር አፄ ናኦድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የተለያዩ ንብረቶችን ማለትም
የተሰባበሩ ወንበሮች ፣
የተለያዩ ኤሌክትሮኒክስ እቃዎች
የተለያዩ ብዛት ያላቸው አሮጌ ወረቀቶችን
በጥቅል ዋጋ ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
በጨረታው ለመካፈል የሚፈልጉ ተጫራቶች የሚከተሉትን ሁኔታዎች በቅድሚያ ማሟላት ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ ግለሰብ በጨረታው መሳተፍ ይችላል።
- ተጫራቾች ሠነዱን ማስታወቂያው ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10/አስር ቀናት ጊዜ ውስጥ ቀርበው መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስረከቢያና ዋስትና የሚያገለግል የመጫረቻ ዋጋ ብር 5,000/አምስት ሺህ/ በባንክ የተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቶች ዕቃዎቹን (ንብረቶች) በት/ቤቱ ግቢ ውስጥ በመገኘት መመልከት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
- ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር የያዘ ሰነድ የማይመለስ ብር 50.00/ ሃምሳ ብር /በመክፈል የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10/አስር/ ተከታታይ ቀናት አፄ ናኦድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን በቢሮ 4 ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በጋዜጣ በወጣበት 11ኛ [በአስራ አንደኛው / የስራ ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አፄ ናኦድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን ቢሮ 4 ይከፈታል።
- የጨረታ ሰነዱ ኦርጅናል እና ኮፒ ተሞልቶና ኦርጅናሉ ኮፒው ተለይቶ በፖስታው ላይ ተፅፎ መቅረብ ይኖርበታል።
- ተጫራቾች በጨረታ የሚያሸንፏቸውን እቃዎች ያሸነፉበትን ጥቅል ዋጋ ለት/ቤቱ ገቢ በማድረግ የጨረታው ውጤት ከተገለፀበት ጊዜ አንስቶ ባሉት5( አምስት ) የስራ ቀናት ውስጥ ዕቃዎቹን በራሳቸው ትራንስፖርት ከት/ቤቱ ግቢ ውስጥ ማንሳት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በጨረታ የሚሸንፏቸውን እቃዎች በተጠቀሰው ጊዜ የማያነሱ ከሆነ የጨረታ ማስከበሪያው ለመ/ቤቱ ገቢ የሚሆን መሆኑን ከወዲሁ እንገልፃለን።
- መ/ቤቱ ለሽያጩ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡- አምስት ኪሎ ቅድስት ማሪያም ሸዋ ዳቦ ፊት ለፊት አፄ ናኦድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን
በአራዳ ክ/ከተማ አፄ ናኦድ የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤት
Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 11፣2013
Deadline:በ11ኛው የስራ ቀን በ4፡00
© walia tender