Tx sl የደባይ ጥላት ግን ወ

Tx sl የደባይ ጥላት ግን ወ

Walia Tender

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በምስራቅ ጐጃም ዞን ገ/ኢ/ል/መምሪያ የደባይ ጥላት ግን ወረዳ የስፖርት ጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል የስፖርት አልባሣት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን፡-

  1. ከላይ በተጠቀሰው የስፖርት አልባሣት የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የግበር ከፋይ መለያ ቁጥር ማስረጃዎች ማያያዝ እንዲሁም የግዥው መጠን 200 ሺህ ብር በላይ የሚሆን ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  2. ተጫራቾች በጨረታው ለመሣተፍ ከላይ የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ መግዣ የማይመለስ 30 ብር በመክፈል ከደባይ ጥላት ግን ወረዳ ገ/ኢ/ ል/ጽ/ቤት ዋና ገንዘብ ያዥ ሰነዱን መውሰድ ይችላል፡፡
  4. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና/ቢድ ቦንድ/ በጥሬ ገንዘብ/በሲፒኦ/ ለሚወዳደሩበት የስፖርት አልባሣት 1,500 ብር ማስያዝ አለባቸው፡፡
  5. ማንኛውም ተጫራች ይህ ማስታወቂያ በአየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ 15ኛው ቀን 11፡00 ድረስ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  6. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሣቡን በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በደ/ጥ/ግን ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ግዥና ንብ/አስ/ቡድን ለዚሁ በተዘጋጀው ጨረታ ሣጥን ዘወትር በሰራ ሰዓት ይህ ማስታወቂያ በአየር ላይ ከዋለበት ጊዜ ጀምሮ እስከ 16ኛው ቀን 3፡00 ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  7. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በደ/ጥ/ግን/ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት በ16ኛው ቀን 3፡00 ታሽጐ በ3፡30 የሚከፈት ይሆናል፡፡
  8. የጨረታ አሸናፊ መሆን የሚቻለው በጥቅል ዋጋ ዝቅተኛ የሰጠ መሆኑ ታውቆ ለሁሉም እቃዎች ዋጋ መሞላት ይኖርበታል፡፡
  9. እቃዎች ገቢ ሲሆኑ በተዘጋጀው የስራ ዝርዝር መሰረት በባለሙያ ተረጋግጦ ገቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
  10. የጨረታ መዝጊያ እና መክፈቻ ቀን በበዓላት ቀን ከሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይሆናል፡፡
  11. አሸናፊ ተጫራች እቃዎችን በደ/ጥ/ግን/ወረዳ ገ/ኢ/ል/ጽ/ቤት ስር ባሉ ንብረት ክፍሎች ገቢ ማድረግ ይኖርበታል፡፡
  12. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  13. በጨረታው ለመሣተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 03 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በፋክስ ቁጥር 058 2570143 በመላክ ወይም በስልክ ቁጥር 058 2570257/035 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡
  14. አሸናፊው ድርጅት ካሸነፈ በኋላ የአሸነፈበትን ጠቅላላ ዋጋ 10 በመቶ ለውል ማስከበሪያ ማያያዝ ይጠበቅበታል፡፡

የደባይ ጥላት ግን ወረዳ የስፖርት ጽ/ቤት


Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013

Deadline:በ16ኛው ቀን 3፡00


© walia tender

Report Page