Tx pr sl fr የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍ/ፍ

Tx pr sl fr የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍ/ፍ

Walia Tender

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የግዥ ፋይናንስ ንብረት አስተዳደር ቡድን በ2013 በጀት ዓመት ለተለያዩ የሥራ ሂደቶች አገልግሎት የሚሰጡ እቃዎችን ለመግዛት

  • ሎት 1 የተዘጋጀ የደንብ ልብስ ፣
  • ሎት 2 ጫማ፣
  • ሎት 3 የህትመት ዉጤቶች፣
  • ሎት 4 የፅህፈት መሳሪያ፣
  • ሎት 5 የጽዳት እቃወች፣
  • ሎት 6 የኤሌክትሮኒክስ እቃዎች እና
  • ሎት 7 የፈርኒቸር እቃዎች ለመግዛት መስፈርቱን አሟልተዉ ከሚገኙ

አቅራቢ ድርጅቶች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /ቲን ነምበር/ የተቀበሉ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉና አግባብ ያለው የንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፣
  3. ተጫራቾች የሚጫረቱት የግዥ መጠን ብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሽህ ብር/ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ ሴት ታክስ /ቫት/ የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማሰረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  5. የሚገዙት የእቃ አይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይችላሉ ከተጠቀሰው ስፔስፌኬሽን ውጭ ሰርዞ ሌላ ስፔስፌኬሽን መቀየር ከውድድሩ ውጭ ያደርጋል፡፡
  6. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 20 (ሃያ )ብር በመክፈል በማዕ/ጎ/ዞ/ከፍ/ፍ/ቤት ማግኘት ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በሎት ድምር ከሞሉት ጠቅላላ ዋጋ 1% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ ከመ/ቤታችን የግዥና ን/አስ/ቡድን ገንዘብ ያዥ በመ/ሂ 1 ለማስያዙ የገቢ ደረሰኝ
  8. አስቆርጦ ከሚወዳደርበት ሰነድ ጋር የደረሠኙን ኮፒ በማሸግ ማስገባት አለበት፡፡ ይህ ሳይሆን ቢቀር ወይም ያስያዙት ሲፒኦ ከ1 በመቶ ቢያንስ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ተጫራቾች ከውድድሩ ውጭ ይሆናል፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ሲሞሉ ስርዝ ድልዝ ሳይኖረው ኦርጅናል እና ኮፒ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ ማዕ/ጎ/ዞን ከፍ/ፍ/ቤት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይችላሉ፡፡
  10. ጨረታው በአየር ላይ ጸንቶ የሚቆይበት ከመስከረም 25/2012 ዓ/ም እስከ ጥቅምት 09/2012 ዓ/ም ድረስ ለ15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱ ይሸጣል፡፡ ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ማዕ/ጎ/ዞን ከፍ/ፍ/ቤት ጥቅምት 10/2012 ዓ/ም ከጧቱ በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ቀን በ4፡30 ሰዓት በግልጽ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በቀኑና በሰዓቱ ካልተገኙ ጨረታዉን ከመክፈት አያግድም፡፡
  11. አሸናፊው እቃዎቹን በራሱ ትራንስፖርት ማቅረብ የሚችል እና የርክክብ ቦታ ሰ/ጎ/ዞ/ከፍ/ፍ/ቤት ን/ክፍል ይሆናል፡፡
  12. ተጫራቾቸ በሚያቀርቡት የማወዳደሪያ ሀሳብ ስማቸውን ፊርማቸውን እና ሙሉ አድራሻቸውን ማስፈር አለባቸው የጨረታ አሸናፊ የሚለየው በሎት ወይም በነጠላ በሞላው ዋጋ ሲሆን ተጫራቾች ሁሉንም ዝርዝር ዋጋ መሙላት አለባቸው ፡፡
  13. የጨረታ መዝጊያ ቀን ከተጠናቀቀ በኋላ ተጫራቾች ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና እራሳቸውን ማግለል አይችሉም
  14. አሸናፊው ተጫራች የእቃዎችን ጥራት በተመለከተ ለሚመለከታቸው ባለሙያዎች ጥራቱን በማረጋገጥ ማስረከብ ግዴታው ነው፡፡ በጥራት አረጋጋጭ ባለሙያ መሰረት የጥራት ችግር ያለባቸውን ሙሉ በሙሉ በመመለስ ትክክለኛ ጥራት ያላቸውን እቃዎች የማቅረብ ግዴታ አለባቸው፡፡
  15. መ/ቤቱ ይህን ጨረታ የተሻለ አማራጭ ካገኘ በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  16. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ አቅራቢዎች ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልጋቸው በስልክ ቁጥር 0584174941 ደዉለዉ መጠየቅ የሚችሉ ሲሆን በተጨማሪም መስከረም 25/2012 የወጣውን በኩር ጋዜጣ መመልከት ይችላሉ፡፡

የሰሜን ጎንደር ዞን ከፍ/ፍ/ቤት


Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013

Deadline:ጥቅምት 10/2012


© walia tender

Report Page