Sl vi mt tx bu ag lb md fr ot የጓንጓ ወረዳ ገ/ኢ

Sl vi mt tx bu ag lb md fr ot የጓንጓ ወረዳ ገ/ኢ

Walia Tender

ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ገ/ኢ/ትብ/ቢሮ የአዊ/ብሔ/አስ/ገ/ኢ/ትብ/ ዋና መምሪያ የጓንጓ ወረዳ ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳድር ቡድን

ለ2013 በጀት አመት

  • ሎት 1 ስቴሽነሪ
  • ሎት 2 ኤሌክትሮኒክስ
  • ሎት 3 የፅዳት ዕቃ
  • ሎት 4 የመኪና ጐማ እና የሞተር ሳይክል ጐማ
  • ሎት 5 የስፖርት አልባስት
  • ሎት 6 የተዘጋጁ ልብሶች
  • ሎት 7 ብትን ጨርቅ
  • ሎት 8 ደንብ ጫማ
  • ሎት 9 የህንፃ መሳረያ
  • ሎት 10 የመኪና ስፔር ፓርት
  • ሎት 11 አፍሬዴቭ ፓንፕ
  • ሎት 12 የስፖርት ቁሳቁስ
  • ሎት 13 ክሎሪን
  • ሎት 14 የአገር ውስጥ ፈርኒቸር
  • ሎት 15 የእንስሳት መድሃኒት እና ቁሳቁስ
  • ሎት 16 የውጭ ፈርኒቸር ግዥ አወዳድሮ መግዛት

ስለሚፈልግ የሚከተሉትን መስፈርቶችን የሚያሟሉ ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሃሳብ እንዲያቀርቡ ይጋብዛል ::

  1. በዘመኑ በዘርፉ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸዉ፣
  2. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን) ማቅረብ የሚችል፣
  3. የሚገዛዉ የግዥ መጠን ከ200‚000.00 ብር እና ከዚያ በላይ ከሆነ የቫት ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባችዋል፣ ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1-3 የተጠቀሱትንና ማስረጃዎችን ማለትም የንግድ ፈቃድ ቲን ሰርተፊኬትና ቫት ሰርተፊኬት የማይመለስ ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ፖስታ ዉስጥ በማስገባት ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል ::
  4. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱ በበኩር ጋዜጣ (በግልፅ ጨረታ) ከወጣበት ከ 25/01/2013ዓ.ም ጀምሮ 09/02/2013 ዓ.ም ከቀኑ 11፡30 ድረስ የጨረታ ሰነዱ ጓ/ወ/ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት የግዥ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 05 የማይመለስ ብር 50.00 (ሀምሳ ብር ብቻ/ መግዛት ይችላሉ::
  5. የማወዳደሪያ ስርዓቱ የጨረታ አሸናፊ የሚለየው በጥቅል ነው::
  6. የሁሉም ጨረታ ሰነድ ዓይነቶች ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፌኬሽን) ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይቻላሉ::
  7. ተጫራቾች የጫራታ ማስከበሪያ ዋስትና (ቢድ ቦንድ) ለሚወዳደሩበት ጠቅላላ ዋጋ ድምር 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲ.ፒ.ኦ) ወይም በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በመ/ቤታችን የገቢ ደረሰኝ /መሂ-1/ገቢ በማድረግ የደረሰኙን ፎቶ ኮፒ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማያያዝ አለባቸዉ::
  8. ማንኛዉም ተጫራቾች የጫራታ ሰነዱን በጥንቃቄ በፖስታ በማሸግ ጓ/ወ/ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት በግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በተዘጋጀዉ የጨረታ ሳጥን በጋዜጣ ከወጣበት እለት ከ 25/01/2013ዓ.ም ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት እስከ 10/02/2013ዓ.ም እስከ 4፡00 የመጫረቻ ሰነዱን ማስገባት ይኖርባቸዋል ::
  9. ጨረታዉ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸዉ በተገኙበት በጓ/ወ ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት ግ/ን/አስ/ደ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 5 በ16ኛዉ ቀን የጨራታ ሳጥኑ ከጥዋቱ 4፡00 ስዓት ታሽጎ 4፡15 ይከፈታል:: ነገር ግን 16ኛዉ ቀን ወይም የሚከፈትበት ቀን ብሔራዊ በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለዉ የስራ ቀን በተመሳሳይ ስዓት ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡15 ይከፈታል::ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎች ካልተገኙ የጨረታ ሰነዱ እንዲከፈት ተደርጎ ያልተገኙ ተጫራቾች ግን በእለቱ ለሚተላለፈዉ ዉሳኔ ተገዥ ይሆናሉ::
  10. ተጫራቾች ንግድ ፍቃዳቸዉ በሚጋብዛቸዉ ብቻ መወዳደር አለባቸው::
  11. ተጫራቾች ያሸነፉበትን እቃ በጓ/ወ/ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት በራሳቸዉ ወጪ በማምጣት በባለሙያና በጥራት አረጋጋጭ ኮሚቴዎች በማስፈተሸ ወይም በማስመርመር የማስረከብ ግዴታ አለባቸዉ
  12. ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ መሙላት የተከለከለ ነዉ ::
  13. ማንኛውም ተጫራች የሚያቀርበው የንግድ ፈቃድ፣ ቲን፣ቫት እንዲሁም ያሚሞላቸው ሰነዶች ለሦስተኛ ወገን በግልፅ የሚታይና የሚነበብ መሆን አለበት::
  14. ማንኛዉም ተጫራች በሚያቀርበው መወዳደሪያ ሀሳብ ስማቸውን ፤ፊርማቸውን እና የድርጅቱን ማህተም ማድረግ አለባቸው::
  15. መ/ቤቱ የግዥውን መጠን 20 በመቶ የመጨመር የመቀነስ መብት አለው::
  16. የሞሉት ዋጋ ማንኛውም ወጪ በራሱ መሽፈን አለበት::
  17. ተጫራቾች በግዥ መመሪያ ተገዥ መሆን አለባቸው::
  18. የሞሉት ዋጋ ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ40 ቀን ፀንቶ ይቆያል::
  19. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታዉን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነዉ::
  20. በጨረታዉ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጫራታዉ ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 0582250506 ፣ 0582250009 በመደወል ማብራሪያ ማግኘት ይችላሉ::

የጓንጓ ወረዳ ገ/ኢ/ትብ/ጽ/ቤት


Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013

Deadline:በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00


© walia tender

Report Page