Sl tx pr vi ot በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 አ
Walia Tenderየጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር፡001/2013
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት ለ2013 በጀት አመት የሚያስፈልጉትን
ሎት 1:-የፅህፈት መሳሪያዎች፣
ሎት 2፡- የፅዳት እቃዎች፣
ሎት 3፡- ልዩ ልዩ መሳሪያዎች፣
ሎት 4፡- የደንብ ልብስ፣
ሎት 5፡- ህትመት፣
ሎት 6፡- የመኪና ጎማ፣
በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ስለሚፈልግ የሚከተለውን የጨረታ መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾችን እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
- ለሎት 1 :-2000 ብር ; ለሎት 2፡- 3000 ብር : ለሎት 3፡2500 ብር : ለሎት 4 ፡-3000 ብር፣ ሎት 5፡ 1500 ብር እና ለሎት 6፡- 2000 ብር በባንክ በተረጋገጠ CP0 ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማያያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ፣የቫት እና የቲን ተመዝጋቢ የሆኑ እና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ እንዲሁም በመንግስት ግ/ን/አስ/ኤጀንሲ ድህረ ገፅ ላይ በአቅራቢዎች ምዝገባ ዝርዝር የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበትእለትጀምሮለ10ተከታታይ የስራ ቀናት የማይመለስ ብር 100 በመክፈል ከል/ክ/ከ/ወረዳ 2 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 16 ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በታሸገ ኤንቨሎፕ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ ለተከታታይ 10 የስራ ቀናት ለጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሳጥን ከመከፈቱ በፊት ለተወዳደሩባቸው ሎት1፣ሎት2፣ሎት3፣ ሎት 4 እና ሎት5 ናሙና ማቅረብ ይኖርባቸዋል ::
- ተጫራቾች በሚወዳደሩባቸው እቃዎች በእያንዳንዱ ነጠላ ዋጋ ላይ ቫት ጨምረው የግድ መሙላት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው አሸናፊ ውል ከተፈፀመበት ቀን ጀምሮ እቃውን በራሱ ትራንስፖርት በሰጠው ናሙና መሰረት ንብረት ክፍል ማስረከብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሀሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው እራሳቸውን ማግለል አይችሉም፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ በአስረኛው(10ኛው) ቀን በ9:00 ሰአት ታሽጎ በእለቱ ከቀኑ 9፡30 ይከፈታል፡፡ የመክፈቻ ቀኑ በአል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰአት ታሸጎ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በወ/2/ፋ/ጽ/ቤት በግ/ን/አስ/ደ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 16 ይከፈታል፡፡
- የዘገየ ጨረታና በጨረታ መክፈቻ ላይ ያልተነበበ ጨረታ ተቀባይነት የለውም ወረዳው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ ፡- ጦር ኃይሎች ወደ 18 በሚወስደው መንገድ 700 ሜ ገባ ብሎ ኪዳኔ ገብሬ ህንፃ 4ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 16 ስልክ ቁጥር፡- 01137133-24 /011-371-33-21
በልደታ ክፍለ ከተማ ወረዳ2
አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት
Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 8፣2013
Deadline: በ10ኛው ቀን 9፡00
© walia tender