Sl bu ot ins የባህር ዳር መንገዶች ባለ

Sl bu ot ins የባህር ዳር መንገዶች ባለ

Walia Tender

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት የመብራት እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የም ትችሉ መሆኑን ይጋብዛል ፡፡

  1. የዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያለው፣
  2. የግብር ከፋይ መለያ/ቲን/ ያላቸው፣
  3. በስሙ የታተመ ማህተምና ደረሰኝ ያለዉ፣
  4. የግዥው መጠን ብር 200,000/ሁለት መቶ ሺህ ብር እና በላይ ከሆነ ተጫራቾች የተጨማሪ ዕሴት ታክስ(ቫት) ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
  5. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተራ ቁጥር 1--3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ኮፒ ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው
  6. የሚገዙ እቃዎች አይነትና ዝርዝር መግለጫ (ስፔስፊኬሽን) ናሙና የቀረበ ስለሆነ የጨረታ ሰነዱን ሲወስዱ ማየት ይችላሉ
  7. ተጫራቾች የጨረታ መስከበሪያ 50,000 ሀምሳ ሽህ/ብር በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ሲፒኦ) ማስያዝ አለባቸው፡፡
  8. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአንድ ወይም አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጅዎች ማለትም ዋናና ቅጅ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግዥ/ንብ/አስ/ቡድን በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ከ25/01/2013 ዓ/ም እስከ 10/02/2013 ዓ/ም ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል
  9. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግዥ/ንብ/አስ/ቡድን በ10/03/2013 ዓ/ም ቀን 8፡30 ታሽጎ 9፡00 ይከፈታል፡፡
  10. አሸናፊዉ የሚለየዉ ጥቅል ድምር ዝቅተኛ ዋጋ ባቀረበ ይሆናል
  11. መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ወይም ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
  12. ተጫራቾች ያሸነፉትን ኦርጅናል ዕቃ በባ/ዳር ከ/አስ/መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት ንብረት ክፍል ድረስ በማጓጓዝ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
  13. በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ በባ/ዳር ከ/አስ/ መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት ግዥ ፋይ/ንብረት አስ/ቡድን ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 058-320-324-6 በመደወል ማብራሪያ መጠየቅ ይቻላል፡፡

የባህር ዳር ከተማ አስተዳደር መንገዶች ባለስልጣን ጽ/ቤት


Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013

Deadline:10/03/2013


© walia tender

Report Page