SL TX VI ደ/ታቦር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
Walia Tender
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሰት ቴክኒክና ሙያ ቢሮ ደቡብ ጐንደር አስ/ዞን የደብረታቦር ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ለቢሮ መገልገያ እና ለመማር ማስተማር አገልግሎት የሚውሉ
ሎት 1. የፅህፈት መሳሪያ ዕቃዎች፤
ሎት 2. ወረቀትና የወረቀት ውጤቶች፤
ሎት 3. ኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ፤
ሎት 4. የፅዳት እቃዎች
ሎት 5.የደንብ ልብስ
ሎት 6 የተሸከርካሪ መለዋወጫ እቃዎች
በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል፡፡
- ተጫራቾች በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸውና ማስረጃውን ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ቲን ያላቸውና ማስረጃውን ማቅረብ የሚችሉ፣
- የግዥ መጠን 200,000 (ሁለት መቶ ሽህ ብር) በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ቫት ከፋይነትን የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ በተ.ቁ 1.-3 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች የሚነበቡ ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፣
- የሚገዙ የዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 50.00. /ሀምሳ ብር / በመክፈል ከግ/ፋ/ን/አ/ቡድን ክፍል ቢሮ ቁጥር 1 ከዋና ገንዘብ ያዥ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ብር የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ ድምር 1.5 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.ኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፣ በጥሬ ገንዘብ ከሆነ በመሂ/1 በመቁረጥ ደረሰኙን ኮፒ አድርገው በጨረታ ፖስታው ውስጥ አሽገው ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሃሳቡን አንድ ወጥ በሆነ በሁለት ቅጂዎች ማለትም ኦርጅናልና ፎቶ ኮፒ በማለት በጥንቃቄ በተለያየ በታሸገ ፖስታ በደ/ታ/ፖ/ቴ/ኮሌጅ በግ/ፋ/ን/አ/ ቡድን ወይም ቢሮ ቁጥር 1 ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ስዓት ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፡፡
- ጨረታው ተጫራቶች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ፋ/ን/አ/ቡድን ክፍል ቢሮ ቁጥር 01 በ16ኛው ቀን በ3፡00 ታሽጎ 3፡30 ይከፈታል፡፡ የጨረታ መክፈቻ ቀን ቅዳሜ እና እሁድ የህዝብ በዓላት ቀን ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ከተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር 20,000 /ሀያ ሽህ ብር/ እና በላይ ሽያጭ ከተፈጸመ 7.5 በመቶ ቫት ይቀንሳል፡፡
- ተጫራቶች የሚወዳደሩበት በቫት ከሆነ የሚሞሉት ዋጋ ቫትን ጨምሮ መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ሰነዱ የተጠቀሰውን መለያ /ስፔስፊኬሽን/ መቀየር ወይም ስያሜ መስጠት ወይም የማስተካከል ስራ ከተሰራ እና ስርዝ ድልዝ ካደረጉት ከውድድሩ ውጭ ይሆናሉ፡፡
- ተጫራቾች ያሸነፉቸውን እቃዎች ከግዥ ፈጻሚው መ/ቤት ድረስ በተጠየቀው ስፔስፊኬሽን መሰረት ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- አሸናፊው የሚለየው በጥቅል/በተናጠል ዋጋ ይሆናል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት በአሸነፈበት ዕቃ የዋጋ ድምር 10 በመቶ የውል ማስከበሪያ ማስያዝ አለበት፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ ሆኖም ጨረታው በመሰረዙ ተጫራቶች ላወጡት ዋጋ ኮሌጁ ተጠያቂ አይሆንም፡፡
- ስለጨረታው ማብራሪያ መጠየቅ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 01 በአካል በመገኘት ወይም በስ-ቁጥር 0584410447 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡
ደ/ታቦር ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
__________________
Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013
Deadline:16ኛው ቀን በ3፡00
__________________
© walia tender