SL TX PR በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 4 አስተዳደር ፋ

SL TX PR በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 4 አስተዳደር ፋ

Walia Tender

የጨረታ ማስታወቂያ 

በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የወረዳ 4 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት በሥሩ ለሚገኙ ጽ/ቤቶች ለ2013 በጀት ዓመት 1ኛ ዙር የሚያስፈልጋቸው

1. የጽህፈት መሳሪያዎችና አላቂ የቢሮ ዕቃዎች ፤
2. ቶነሮች ፤
3. የጽዳት ዕቃዎች፤
4 የደንብ ልብሶች ፤
5. ብትን ጨርቆች ፤
6. የደንብ ልብስ ስፌት፤
7. ህትመት ፣ እና
8.የስፖርት ዕቃዎችን

አጫርቶ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በዚሁ መሰረት በጨረታ መወዳደር የምትችሉ፡

  1. የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላችሁ 
  2. የዘመኑን ገቢ ግብር አጠናቀው የከፈሉ
  3. የአቅራቢነት የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት የሚያቀርቡ /ከአቅራቢነት ያልተወገዱ መሆን አለባቸው 
  4. ቫት/TOT የተመዘገቡና የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ
  5. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተመሰከረለት CPO በሚያቀርቡት ገንዘብ ዋጋ ለጽህፈት መሳሪያዎችና አላቂ የቢሮ ዕቃዎች ብር 2200.00 ፣ ለቶነር ብር 1500.00፤ ለጽዳት ዕቃዎች ብር 3500.00፤ ለደንብ ልብሶች ብር 2500.00፤ ለብትን ጨርቆች ብር 2000.00፣ለደንብ ልብስ ስፌት ብር 1500.00፤ ለህትመት ብር 600.00 እና ለስፖርት ዕቃዎች ብር 500.00 ማቅረብ አለባቸው ፤ 
  6. የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 (አንድ መቶ ብር ብቻ) ለ አንድ ሎት መክፈል አለባቸው፣ ከአንድ ሎት በላይ የሚገዙ አቅራቢዎች ተጨማሪ በሚገዙት በያንዳዱ ሎት 50 ብር ለመክፈል ይገደዳሉ ፤ 
  7.  ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 10 ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ በወረዳ 4 ፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ዋና የስራ ሂደት በመቅረብ የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ሰነድ በእያንዳንዱ ገጽ ላይ ፊርማና ማህተም በማሳረፍበታሸገ ኤንቨሎፕ ማስገባት ይጠበቅባቸዋል፡፡ 
  9. ተጫራቾች ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የሥራ ቀናት በአ/ከ/ክ/ከ/ወረዳ 4 ፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሉት ዋና የስራ ሂደት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል ፤
  10. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ዋና እና ኮፒ እንዲሁም የቴክኒካል ሰነድ ለየብቻ በማሸግ ሙሉ አድራሻ በትክክል በመሙላት ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው ፤ 
  11. የጨረታ ሰነዱ በተጫራቾች መሞላት ያለበት በሙሉ መሞላት አለባቸው፤ 
  12. የጨረታ ሰነዱ እና የዋጋ ማቅረቢያው ሳይለወጥና ሳይቀነስ በሙሉ የማይመልስ አቅራቢ ከጨረታው ይሰረዛል ፤
  13. . ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚያውኑ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ጀምሮ ሎት 1-2፤ በሚቀጥለው ቀን ሎት 3-4 እና በ3ኛው ቀን ከሎት 5-9 ያሉ የሚከፈቱበት ይሆናል፡፡ 
  14. በተራ ቁጥር 13 ላይ የተጠቀሰው በሎት የመከፋፈል ስራ ይመች ዘንድ ከአንድ ሎት በላይ የሚሳተፉ ተጫራቾች ለብቻ ማሸግ አለባቸው፤ 
  15. ተጫራቾች ጨረታው ከመከፈቱ 2 ቀን በፊት ለሁሉም ዕቃዎች ናሙና ወይም ስፔስፊኬሽን ወይም ፎቶ ወይም ማንኛውም ስለ ዕቃው የሚገልጽ መረጃ ማቅረብ መቻል አለባቸው፤ የናሙና መቀበያ ቅጽ በ2 ኮፒ አዘጋጅቶ አብሮ ማቅረብ መቻል አለባቸው፡፡ 
  16. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ነጠላዋጋ ከVAT TOT በፊት ያለ ስርዝ ድልዝ በትክክል መሞላት አለበት
  17. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ነጠላ ዋጋላይ የማይነበብና ስርዝ ድልዝ ያለው ከሆነ ተቀባይነት የለውም፡፡ 
  18. ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታ ራሱን ማግለል አይቻልም ፣ 
  19. መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡ 
  • አድራሻ፡ ከአውቶቢስ ተራ ወደ አጣና ተራ በሚወስደው መንገድ ኢትዮ ጠቢብ ሆስፒታል ፊት ለፊት 100 ሜትር ገባ ብሎ ሠፈረ ሰላም ት/ቤት ፊት ለፊት በአ/ከክ/ከ/ወረዳ 4 አስተዳደር ህንጻ ምድር ላይ ፋይናንስ ጽ/ቤት የግዥና ንብረት አስተዳደር ጠቅላላ አገልግሎት ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 4 
  • ስልክ ቁጥር፡- 011-827-71-97 /011-827-6260 

በአዲስ ከተማ ክፍስ ከተማ ወረዳ 4 አስተዳደር ፋይናንስ ጽ/ቤት 

__________________

Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 8፣2013

Deadline:በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00

__________________
© walia tender


Report Page