OT የይ/ዴንሣ ወረዳ ገጠር

OT የይ/ዴንሣ ወረዳ ገጠር


Walia Tender

የደን ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ

በምዕራብ ጐጃም ዞን የይ/ዴንሣ ወረዳ ገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ጽ/ቤት በአዴት ከተማ አስተዳደር የ01 እና የ02 ቀበሌ ልዩ ስሙ ጽራፂዮን ባታ አካባቢ እና ምንጭት አካባቢ የሚገኘውን ምድብ 01 ፣ ምድብ 02 ፣ ምድብ 03፣ ምድብ 04፣ የለማ የማህበረሰብ ደን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል ፡፡

ተወዳዳሪዎች ማሟላት የሚገባቸው መመዘኛዎች፣

  1. ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  2. ተጫራቾች የቲን/የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
  3. ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጎ ከ200 ሺህ ብር በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ/ቫት/ ተመዝጋቢ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
  4. ለጨረታ የቀረበውን ደን ማየት የሚፈልጉ ተጫራቾች ለዚሁ ሲባል በተዘጋጀው የመጫረቻ ሰነድ ላይ በተገለፀው ቦታ ድረስ በመሄድ ጨረታው ለመጀመሪያ ጊዜ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ20 የስራ ተከታታይ ቀናት ማየት ይችላሉ፡፡
  5. የተዘጋጀውን የመጫረቻ ሰነድ ጨረታውን ባወጣው መ/ቤት ቢሮ ቁጥር 03 በመንግስት የስራ ሰዓት በመገኘት ለአንዱ የጨረታ ሰነድ ብር 300 ብር ከፍሎ መግዛት ይችላል፡፡
  6.  የመጫረቻ ሰነዱ ከ25/01/2013 ዓ/ም እስከ 20/02/2013 ዓ/ም ከቀኑ 6፡30 ለ20 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ የሚቆይ ሲሆን የተሞላውን የዋጋ መሙያ ፣ቲን ፣ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድና ሌሎች ማስረጃዎችን በታሸገ ፖስታ አሽጎ ማህተም በማድረግ በተዘጋጀው ሣጥን ማስገባት አለበት፡፡
  7. ጨረታው የሚዘጋበት በ20/02/2013 ዓ/ም በ8፡00 ሲሆን ጨረታው የሚከፈተው በተዘጋበት እለት በ20/02/2013 ዓ/ም በ9፡00 ቢሮ ቁጥር 03 ፍላጐት ያለው ተጫራች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ 
  8. ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በጨረታ መክፈቻ እለት ባይገኙ መ/ቤቱ ጨረታውን ለመክፈት የሚገድበው/የሚከለከለው/ የለም፡፡
  9.  ተጫራቾች የሚጫረቱበትን የደን ዓይነት ለመግዛት የሞሉትን ዋጋ 10 በመቶ የጨረታ ማስከበሪያ/ቢድ ቦንድ/ በባንክ ክፍያ ማዘዣ/ሲፒኦ/ ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያው ለእያንዳንዱ የደን ምድብ ወይም በጥቅል መቅረብ ይኖርበታል ፡፡
  10. ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጉት የእያንዳንዱ የደን ዓይነትና መጠን እና የሚገዙበትን ዋጋ ከስማቸውና ከአድራሻቸው ጋር በተናጠል በታሸገ ኢንቨሎፕ በማሸግ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት የምዕ/ጐጃም ዞን የይ/ዴ/ወረዳ ገጠር መሬት አስተዳደርና አጠቃቀም ጽ/ቤት የማህበረሰብ ደን ጨረታ ተብሎ በጉልህ ከተፃፈበት በኋላ ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በመቁጠር እስከ 20ኛው ቀን 11፡30 በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  11. ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0583380370 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
  12. ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሰው ማቅረብ አይችሉም፡፡
  13.  አሸናፊው ድርጅት አሸናፊነቱ ከተገለፀለት ቀን ጀምሮ ከ05 የስራ ቀናት በኋላ ባሉት 05 ተከታታይ ቀናት ውስጥ 10 በመቶ ውል ማስከበሪያ በማስያዝ ውል መያዝ ይኖርበታል፡፡ 
  14.  ጨረታውን የምናወዳድረው በተናጠል/በድምር/ ዋጋ ነው፡፡
  15.  ማንኛውንም ወጭ ተጫራች/ገዥዎች/ የሚሸፍን መሆን አለበት፡፡
  16.  መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  17.  የጨረታውን ሂደት ለማዛባት የሚደረግ ህጋዊ ያልሆነ ማንኛውም የተጣራቾች ሂደት ካለ ከውድድር ውጭ ይደረጋል፡፡

የይ/ዴንሣ ወረዳ ገጠር መሬት አስተዳደር እና አጠቃቀም ጽ/ቤት

__________________


__________________
© walia tender

Report Page