LB MD የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
Walia Tenderየግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር 027/2012 ዓ.ም
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ ለሆስፒታሉ ግብአት አገልግሎት የሚውሉ
ሎት 1 ኦክስጅን የተሞላ ሲሊንደር ግዥ
2 መድኃኒቶች እና የህክምና መገልገያ ግብአቶች
- በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፍቃድ ያላቸው መሆኑ በዘርፉ የተሰማሩ ለመሆናቸው በጀርባው ይመልከቱ የሚል ጽሁፍ ያለው፣
- የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ፣
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ የታደሰ የዘመኑን ንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ እና የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
- ለመንግስት መ/ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው። እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ክሪላንስ ማቅረብ አለባቸው::
- አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም፤ ጨረታው 10 የስራ ቀናት ከ2፡30 ሰዓት እስከ11፡00 መግዛት ይቻላል።
- በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታው ውጤት እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን ገንዘብ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና 2 ፐርሰንት የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቶች ቴክኒካል ሰነዶች እና የዋጋ ማቅረቢያዎች ፋይናንሻል/ ሰነዶችን በተለያዩ ፖስታ ታሽገው ለየብቻ መቅረብ አለባቸው። ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዶችን በአንድ ላይ አሽጎ ያቀረበ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከጨረታ ውጪ ይሆናል::
- ማንኛውም ተጫራች የሚያስገባውን ሰነድ ፋይናንሻል ኮፒና ኦርጅናል እንዲሁም ቴክኒካል ኮፒና ኦርጅናል በማድረግ በተለያዩ ፖስታዎች አሽጎ ለየብቻ እያንዳንዱን በማህተም በመምታትና የሚወዳደሩበትን ሎት በመጻፍ በጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጨራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያስይዙት ሲፒኦ ከቴክኒክ ሰነዶች ጋር በአንድ አሽገው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ 200 ብር በመክፈል መግዛት ይችላሉ::
- ተጫራቾች ዋጋ ሲሞሉ ከቫት ጋር መሆን አለበት። ይህ ካልሆነ ግዢ ፈጻሚው የተሞላው ዋጋ ከነቫቱ እንደሆነ በመቁጠር ያወዳድራል::
- ጨረታው የሚከፈተው ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በሚቆጠር በ10 የስራ ቀናት ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በቀጣዩ የስራ ቀን በ4 ፡00 ሰዓት ተጫራቾች በተገኙበት በመ/ቤቱ አዳራሽ ይከፈታል::
- የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ የሚደርስ ማንኛውም ሰነድ ሳይከፈት ለተጫራቹ ይመለሳል::
- ሆስፒታሉ ሌላ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል መሰረዝ ይችላል::
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 0946670707 በመደወል መጠየቅ ይቻላል::
- አድራሻ 6ኪሎ የካቲት 12 ሰማእታት ሃውልት ፊት ለፊት
የካቲት 12 ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
__________________
Posted:አዲስ ዘመን መስከረም 8፣2013
Deadline:በ10 የስራ ቀናት ከቀኑ 11፡00
__________________
© walia tender