CN INS ENG MECOD 17
Walia Tenderየጨረታ ማስታወቂያ
በመከላከያ ኮንስትራክሽን ኢንተርፕራይዝ የአርሚ ፋውንዴሽን አፓርትመንት ግንባታ ፕሮጀክት /16-01B ምዕራፍ ሁለት በሰሚት አካባቢ ለሚሰራቸው የህንፃ ግንባታ የሚከተሉትን ሥራዎች እና አቅርቦት በሚቀርበው ዝርዝር መሰረት በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል::
- Cementious type of Water Proofing work for septic tank
- Membran type of Water Proofing Work for pump house
ስለሆነም ተጫራቾች ለእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ/ ብቻ ከፍለው ከፕሮጀክቱ ፋይናንስ ክፍል በመውሰድ በተያያዘው የሥራ ዝርዝር መሰረት የሚሰሩበትን/የሚያቀርቡበትን ዋጋ በመሙላት በፖስታ አሽገው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 7 /ሰባት/ የሥራ ቀናት ቅዳሜን ጨምሮ በፕሮጀክቱ ግቢ የግብአት አቅርቦት እና አስተዳደር ኬዝ ቲም ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው ጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው:: ጨረታው ሰኞ 02/2/2013ዓ/ም ከረፋዱ 4.00 ሰዓት ይዘጋል:: ቴክኒካል ዶክመንት በዕለቱ 4.30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን የፋይናንሻል ሰነድ የሚከፈትበት ቀን በውስጥ ማስታወቂያ የሚገለጽ ይሆናል::
ተጫራቾች ማሟላት ያለባቸው መስፈረት:-
- ተጫራቾች ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ ለተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ እና TIN No ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው::
- ተጫራቾች በጨረታው መሳተፍ የሚችሉ መሆናቸውን የሚገልፅ ታክስ ክሊራንስ (tax clearance) ከግብር ሰብሳቢ መ/ቤት ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሚያቀርቡት የገንዘብ መጠን በተጫራቾች መመሪያ ላይ በተጠቀሰው መሠረት መሆን አለበት::
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ የዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ በመሙላት የድርጅቱን ማህተም፣ ፊርማ እና መራ ስም እንዲሁም አድራሻቸውን በመግለፅ በታሸገ ኢንቨሎፕ ማቅረብ ይኖርባቸዋል::
- ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉት በዘርፉ ፈቃድ ያላቸው መሆን አለበቸው::
- በውሃ ስርገት ሥራ (Water Proofing Work) ላይ ልምድ ያለው መሆን አለበት
- ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ሰነዱ ለየብቻ ታሽጐ መቅረብ አለበት::
- የሥራው መጠን ሊጨምር ወይም ሊቀንስ ይችላል::
- ቴክኒካል ሰነድ በእለቱ የሚከፈት ሲሆን ፋይናሻል የሚከፈትበት ቀን ለተጫራቾን በውስጥ ማስታወቂያ ይገለጻል::
- ጨረታውን አሸናፊ ሆነው ሲገኙ ከጠቅላላ ዋጋው 10% የመልካም ሥራ አፈጻጸም ዋስትና (Unconditnal Bank Guarantee ማስያዝ የሚችሉ መሆን አለባቸው
- ፕሮጀክቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
አድራሻ፡- ሰሚት ኮንዶሚኒየም 2ኛ በር ከጊዮርጊስ ቤተክርስትያን ወረድ ብሉ
ስ/ቁ 0118-34-92-41
__________________
Posted:ሪፖርተር መስከረም 24፣ 2013
Deadline:02/2/2013
__________________
© walia tender