Bu የግንደወይን ከተማ ውሃ አገ/ጽ

Bu የግንደወይን ከተማ ውሃ አገ/ጽ

Walia Tender

ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ

በምስራቅ ጎጃም ዞን በጎንቻ ሲሶ እነሴ ወረዳ የግንደወይን ከተማ ውሃ አገ/ጽ/ቤት የቧንቧ መገጣጠሚያ እቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉን መሆኑን ይገልፃል፡፡

  1. በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
  2. የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
  3. የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር/ቲን/ ያላቸው፣
  4. የግዥ መጠን ብር 50 ሺህ እና በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ/ቫት/ ማያያዝ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች በጨረታው ለመሣተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1-4 የተጠቀሱትን እና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
  6. የሚገዙ እቃዎችን አይነትና ዝርዝር መግለጫ/ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ መግዣ የማይመለስ ብር 200 ብቻ በመክፈል ሰነዱን ከገ/ያዥ ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 1 በመቶ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ/ሲፒኦ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ደረሰኝ ማስያዝ አለባቸው፡፡
  9. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጅናል እና ኮፒ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ አንድ ፖስታ ግ/ወይን ከተማ ውሃ አገ/ጽ/ቤት የገቢ ግ/ፋ/ን/አስ/የስራ ሂደት በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማለትም ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግ/ወይን ከተማ ውሃ ፍሣሽ አገ/ጽ/ቤት የገቢ ግ/ፋ/ን/አስ/የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 4 በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡30 ታሽጐ 4፡00 ላይ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ካልተገኙ ግን በሌሉበት በተጠቀሰው ቀንና ሰዓት ጨረታው የሚከፈት መሆኑን
  11. ጨረታው ውድቅ ቢሆን ተጫራቾች/ ህጋዊ ወኪሎች/ ያወጡትን ወጭ ጽ/ቤቱ የጠያቂ አይሆንም፡፡
  12. አሸናፊ ድርጅቱ ያሸነፋቸውን እቃዎች ግ/ወይን ከተማ ውሃ ፍሣሻ አገ/ጽ/ቤት ድረስ በራሱ ትራንስፖርት ወጭ ማቅረብ የሚችል መሆኑን እንገልፃለን፡፡
  13. መ/ቤቱ አሸናፊውን የሚለየው በጥቅል ዝቅተኛ ዋጋ ሞልቶ ያቀረበውን ይሆናል፡፡
  14. መ/ቤቱ አሸናፊው ድርጅት ከውል በፊት ያሸነፋቸውን እቃዎች 25 በመቶ የመጨመር/የመቀነስ/ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
  15. በመ/ቤቱ በእቃ ጥራት ባለሙያ እየተረጋገጡ ከመ/ቤቱ እቃ ግምጃ ቤት ንብረት ክፍል ጋር ርክክብ የሚፈፀም ይሆናል፡፡
  16. የጨረታ መክፈቻ ቀኑ በዓል/ቅዳሜና እሁድ/ ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት የሚከፈት መሆኑን ጽ/ቤቱ ይገልፃል፡፡
  17. ካሸናፊ ድርጅቱ 2 በመቶ የቅድመ ግብር የሚቆረጥ መሆኑን፡፡
  18. አሸናፊው ድርጅት ማሸነፉ ከተገለፀለት ቀን ከ6 ቀን ጀምሮ ቀርቦ ውል መያዝ አለበት፡፡
  19. አሸናፊው ድርጅት ማሸነፉ ተገልፆለት ውል ከተፈፀመ በኋላ እስከ 10 ቀናት ውስጥ እቃውን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ በጽ/ቤቱ ውስጥ ካለው እቃ ግምጃ ቤት ማስረከብ ይኖርበታል፡፡ ነገር ግን ድርጅቱ ያሸነፋቸውን እቃዎች ካላቀረበ መ/ቤቱ የውል ማስከበሪያውን ይወርሣል፡፡
  20. አሸናፊው ድርጅት እቃውን ሙሉ በሙሉ አጠናቆ በጽ/ቤቱ ውስጥ ካለው እቃ ግምጃ ቤት ካስረከበ በኋላ በሚቀርበው ህጋዊ የንብረት ገቢ ደረሰኝ መሰረት ክፍያው የሚፈፀምለት ይሆናል፡፡
  21. ተጫራቾች የዕቃ ናሙና ከጽ/ቤቱ ማየት ይችላሉ፡፡
  22. መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ሲሆን ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው/ በጨረታው በሚያወጡት ወጭ መ/ቤቱ ኃላፊነቱን የማይመስድ መሆኑን ማወቅ ይኖርባቸዋል፡፡
  23. በሌሎች ተጫራቾች ዋጋ ላይ ተንተርሶ መጫረት /አንድ ተጫራች/ ከአንድ በላይ ጨረታ ሞልቶ ቢገኝ ከተጫራች ውጭ ያደርጋል/ይሆናል/
  24. በጨረታው ለመሣተፍ የሚፈልጉ ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ገቢ ግዥና ፋ/ን/አስ/የስራ ሂደት በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0586640373/0586640675 በመደወል ዝርዝር መረጃውን ማግኘት ይቻላል፡፡

ማሣሰቢያ መ/ቤቱ ተጫራቾች የሞሉትን ዋጋ ቫትን ጨምሮ እንደሆነ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡

የግንደወይን ከተማ ውሃ እና ፍሣሽ አገ/ጽ/ቤት


Posted:በኩር መስከረም 25፣ 2013

Deadline:በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡30


© walia tender

Report Page