*/

*/

Source

ከእለታት አንድ ቀን አንድ ሙሥሊም ያልሆነ ሰው ሙሥሊም የሆነን ሰው እቤቱ ተቀብሎ አስተናገደ። ‌

ከዚያም ሰውዬው ለሙሥሊሙ ወይን አቀረበለትና ሙሥሊሙም ወይኑን በላ። በመቀጠልም የወይን ጠጅ አቀረበለት፤ ከዚያም ሙሥሊሙ እንዲህ አለው፡- ‌ ሙሥሊሙ፡- “ይህ እኛ ላይ እርም (ሀራም) ነው” አለው። ‌ ሰውዬውም፡- “እናንተ ሙሥሊሞች ትገርማላችሁ፤ ይህን ሀላል ታደርጋላችሁ ይህን ደግሞ ሀራም ታደርጋላችሁ። ሆኖም ግን ይህ ወይን ጠጅ የተሰራው ከዚሁ ከበላኸው ወይን ነው” አለው። ‌ ሙሥሊሙ፡- “ሚስት አለህ?” አለው ‌ ሰውዬው፡- “አዎን” አለው ‌ ሙሥሊሙ፡- “አምጣልኝ” አለውና አመጣለት፤ በመቀጠልም “ሴት ልጅ አለህ?” አለው ‌ ሰውዬው፡- “አዎን” አለው ‌ ሙሥሊሙ፡- “እሷንም አምጣልኝ” አለውና አመጣለት። ከዚያም ሙስሊሙ እንዲህ አለው:- “አየህ ይህችን ሚስትህን አላህ ልታገባት ሀላል አደረገልህ፤ ይህችን ልጅህን ግን ልታገባት ሀራም አደረገብህ። ሆኖም ግን ይህቺ ልጅህ ከዚህች ሚስትህ ነው የተፈጠረችው” አለው። ‌ ሰውዬው፡- “አሽሃዱ አንላኢላሃ ኢለላህ ወአነ ሙሐመደን ረሱሉላህ” በማለት ኢሥላምን ተቀበለ። ‌

ከዚህ ቂሳ ምን ተማራችሁ?

Report Page