*/
Fromአዳዲሶቹ የብር ኖቶች ምስሎች ከቀረቡ በዃላ በሚዲያዎቻችን ሰሞኑን የሚኖሩ ትንታኔዎች
==> የፋሲል ግንብ ከ50 ወደ መቶ ብር መሸጋገሩ የነፍጠኛው ስርዓት ጭራሽ የልብ ልብ እንደተሰጠውና እያደገ እንደሚገኝ ማሳያ ነው። ኦኤምኤን ቲቪ
==> ከፋሲል ግንብ ጎን የሚገኘው የአክሱም ሃውልት በቁመት ከፋሲል እንዲበልጥ የተደረገው አማራን አንገቱን ለማስደፋት ታስቦ መሆኑን ሁላችንም ልንረዳ ይገባል። አስራት ቲቪ
==> በ2 መቶ ብሩ ላይ የሚታየው የተቆራረጠ የኢትዮጵያ ካርታ ኢትዮጵያን ለመከፋፈል ያላቸውን ድብቅ ምኞት በገሃድ ያሳየ ነው። መረጃ ቲቪ
==> ከአረብ የተሰደዱ ሙስሊሞች የገነቡትን የሀረር ግንብ በብር ኖት ላይ ማስፈር አባቶቻችን ያወረሱንን ሃይማኖት ለማጥፋት እየተሰራ ያለውን ስራ የሚያሳይ ነው። ርዕዮት ሚዲያ
==> በሻዐቢያ አርማ ላይ የሚገኝ ግመልን የሀገሪቱ ገንዘብ ላይ ማተም አሃዳዊው አብይ የኢሳያስ ተላላኪ መሆኑን በገሃድ ያሳየ ነው። ድምፀ ወያኔ ቲቪ
==> በብር ኖቶቹ ላይ የፋሲል ግንብ፣ የሶፍ ኡመር ወሻ፣ የአክሱም ሃውልት፣ የሀረር ግንብና ግመል መኖሩ ህብረብሄራዊነታችንን የሚያሳይ መሆኑን አንዳንድ የአዲሳባ ነዋሪዎች ተናገሩ። ኢቲቪ