..

..



ሱራፌል፡- የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ

ዋንጫን እኛ አላጣነውም አሁንም ራሳችንን

እንደሻምፒዮና ቡድን አድርገን ነው

እየቆጠርን የምንገኘውና የእሁዱን የጥሎ

ማለፍ ዋንጫ ማግኘታችን ሁላችንንም

ደስተኛ አድርጎናል፡፡

ሀትሪክ፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

አሸናፊ የተባለው ፋሲል ከነማ ሳይሆን

መቐለ 70 እንደርታ ተብሏል፤ አንተ ግን

ሻምፒዮናው እኛ ነን እያልክ ነው፤ ከምን

በመነሳት ነው?

ሱራፌል፡- የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ

የዘንድሮ የውድድር ዘመን ተሳትፎአችን

ላይ ክለባችን ብዙ ጥሮ ብዙ ለፍቶ ብዙ

መስዋዕትነት ከፍሎ ሽረ ላይ ከኳስ በወጣ

እና በታየው አስቀያሚ ነገር ይኸውም

እግር ኳሳዊ ባልሆነ ሁኔታ በዕለቱ

ፖለቲካዊ ነገሮች በተንፀባረቀበት ሁኔታ

ዋንጫውን ከመድረክ ባንቀበልም አሁንም

በድጋሚ መናገር የምፈልገው የውድድሩ

አሸናፊ እንደሆንን የምንቆጥረው ራሣችንን

ነው፡፡

ሀትሪክ፡- ፋሲል ከነማ በአፍሪካ

ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ ይሳተፋል፤

ስለውድድሩ ተሳትፎ እና ስለሚመዘገበው

ውጤት ምን ትላለህ?

ሱራፌል፡- የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን

ካፕ ላይ ቡድናችን የሚኖረው ተሳትፎ

ከውድድሩ ባሻገር ለእኛም ተጨዋቾች

የፕሮፌሽናል ተጨዋቾችንን ዕድል

የሚያስገኝልን ስለሆነ ለጨዋታው እየሰጠን

ያለው ትኩረት ከፍ ያለ ነው፤ ለውድድሩም

በአጭር ጊዜ ውስጥ ዝግጅታችንን እንጀ

ምራለን፤ የአፍሪካ ኮንፌዴሬሽን ካፕ ላይ

በሚኖረን ውድድርም ቡድናችን ግጥሚ

ያውን የሚያደርገው ለተሳትፎ ሳይሆን

የፋሲል ከነማ እግር ኳስ ክለብ እሁድ እለት ሐዋሳ ከተማን አሸንፎ የኢትዮጵያ ጥሎ ማለፍ ዋንጫን ካነሳ

በኋላ የቡድኑ አሰልጣኝ ውበቱ አባተ እና የቡድኑ ተጨዋች

ሱራፌል ዳኛቸው ስለ ድሉ እና ሌሎች ላቀረብንላቸው ጥያቄ

የሚከተለውን ምላሽ ሊሰጡን ችለዋል፡፡

ጥሩ ውጤት ለማምጣት ነው፤ ፋሲል ከነማ

ጠንካራ እና ጥሩ አቅም ያለው ቡድን

ነውና ለመጀመሪያ ጊዜ በሚኖረን ተሳትፎ

እኛነታችንን ማሳየት እንፈልጋለን፤ ይሄ

እንደሚሳካልንም አምናለሁ፡፡

ሀትሪክ፡- ፋሲል ከነማ የጥሎ

ማለፉን ዋንጫ ያነሳበትን ጨዋታ እንዴት

ትመለከተዋለህ?

ሱራፌል፡- የሐዋሳ ከነማ ክለብን በፍፁም

ቅጣት ምት ያሸነፍንበት ጨዋታ ሜዳው

የአንድ ሁለት ቅብብልንም ሆነ ድሪብል

አድርገህ ጥሩ ለመጫወት የማትችልበት

ነበርና በዚህ በኩል በእንቅስቃሴው በኩል

ተቸግረናል፡፡ ያም ሆኖ ግን ሀዋሳዎች ግብ

በማስቆጠር እኛን ቢቀድሙንም ቡድናችን

ጎል እንደሚያስቆጥር ለአሰልጣኛችን ውበቱ

አባተ እየነገርኩት ነበርና ያንን ነው

በማሳካት በመጨረሻም በፍፁም ቅጣት ምት

ለማሸነፍ የቻልነው፡፡


Report Page